Datasets:
category
stringclasses 4
values | headline
stringlengths 17
80
| text
stringlengths 1
16.8k
| url
stringlengths 36
49
|
|---|---|---|---|
sports
|
የስፖርት ኮከቦች እና የንግድ ምልክቶቻቸው- ከቦልት እስከ ክርስቲያኖ ሮናልዶ
|
የአትሌቲክሱ ዓለም ኮከብ እና ፈጣኑ ሰው ዩሴን ቦልት ከውድድር በፊት እና በኋላ የሚያሳየውን ታዋቂ የሆነውን ምልክት ለንግድ ምልክትነት ለመጠቀም ጥያቄ በማቅረብ ላይ ይገኛል። እሱ ብቻ ግን አይደለም የሚለይበትን ምልክት የሚያሳይ ኮከብ። የአሜሪካ የፓተንት እና የንግድ ምልክት ቢሮ እንደገለጸው ቦልት ታዋቂውን ምልክቱን በንግድ ምልክትነት ለማስመዝገብ ማመልከቻውን ነሐሴ 2014 ዓ.ም. መጀመሪያ ላይ አስገብቷል። መቀመጫቸውን ዋሽንግተን ያደረጉት የንግድ ምልክት ጠበቃው ጆሽ ገርበን “አንድ እጁ ታጥፎ ወደ ጭንቅላቱ ሲጠቆም ሌላኛው እጁ በተመሳሳይ አቅጣጫ ወደ ላይ ከፍ ብሎ እንደሚዘረጋ” ያሳያል ብለዋል። ቦልት ይህን የሚያደርገው ዝነኛ የድል አድራጊነቱን የሚያሳየውን አርማ የንግድ ምልክት በማድረግ ልብሶችን እና የፋሽን ዕቃዎችን ለመሸጥ በማሰቡ ነው። ታዋቂዋ የአሜሪካ የሴቶች ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች ሜጋን ራፒኖ ጎል ካስቆጠረች በኋላ ደስታዋን በምትገልጽበት የተለየ መንገድ ትታወቃለች። ከአሜሪካ የሴቶች ብሔራዊ ቡድን ጋር የዓለም ዋንጫ እና የኦሎምፒክ ወርቅ አሸናፊ ለመሆን የበቃችው ሜጋን እጆቿን ዘርግታ በምታሳየው ፈገግታ ወይም እርካታ ትለያለች። እአአ በ2019 በፊፋ ኮከብ ተጫዋች ለመሆን የበቃችው ተጫዋቿ ቀላል እና በአድናቂዎች የተወደደ የደስታ አገላለጽ ነው ያላት። ሞ ፋራህ የበርካታ የኦሎምፒክ፣ የዓለም እና የአውሮፓ የረዥም ርቀት ሩጫዎች ሻምፒዮን ነው። ብዙዎችም "የእንግሊዝ የምንግዜም ታላቅ አትሌት" እያሉ ይጠሩታል። ውድድሮችን ሲያሸንፍ "ሞቦት" በማሳየት በጣም ታዋቂ ነው። የሁለቱን አጅቹን ጣቶች በማገናኘት የጭንቅላቱ አናት ላይ በማድረግ የስሙ መነሻ የሆነውን ‘M’ የእንግሊዘኛ ፊደል ይሠራል። ታዋቂው ፖርቹጋላዊ የማንቸስተር ዩናይትድ አጥቂ ጎል ካስቆጠረ በኋላ ደስታውን የሚገልጽበት መንገድ አዘጋጅቷል። ይሮጥና ይዘላል፣ አየር ላይ እያለ ይዞርና እጆቹን ወደ ጎን እየወረወረ “ሲ” እያለ ይጮሃል። “ሲ” በፖርቹጋል ቋንቋ አዎ እንደማለት ነው። ደቡብ ኮሪያዊው የእግር ኳስ ኮከብ ሶን ሄንግ-ሚን በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ለሚሳተፈው ቶተንሃም ሆትስፐርስ ይጫወታል። አጥቂው ጎል ካስቆጠረ በኋላ ደስታውን የሚገልጽበት የራሱን ልዩ ምልክት አዘጋጅቷል። አውራ እና ጠቋሚ ጣቶቹን በማገናኘት ያንን ቅጽበት ለመቅረጽ የሚረዳውን ካሜራን የሚወክል ቅርጽ ይሠራል። ስለእነዚህ ምልክተቶች ምን ያስባሉ? ቦልት ዝነኛ ምልክት ያለው ብቸኛው ሰው ባይሆንም በዓለም ዙሪያ በጣም ታዋቂው ነው ማለት ግን ይቻላል። የንግድ ምልክት ማመልከቻው ከተሳካ ደግሞ ምናልባት የበለጠ ዕውቅና ያገኛል።
|
https://www.bbc.com/amharic/articles/ceknk30j2xxo
|
sports
|
እግር ኳስ፡ ዩናይትድ፣ አርሴናል፣ ቼልሲ . . . ምን አስበዋል?
|
የስፖርት ጋዜጦች ስለ እግር ኳስ ምን እያሉ ነው? በሚቀጥለው ጥር የሚከፈተው የዝውውር መስኮትስ ምን ያሳየን ይሆን?ዋና ዋናዎቹን በዚሀች አጭር ዘገባ እንዳስሳለን። አላንድ፡ የቦሩሲያ ዶርትመንዱ አጥቂ ኧርሊንግ ብራውት አላንድ ፈላጊው በዝቷል። አሁን ደግሞ ቼልሲዎች ተጫዋቹን ለማስፈረም ዕቅድ እንዳላቸው እየተነገረ ነው። ነገር ግን ማንቸስተር ሲቲዎች ተጫዋቹ የእኛ ነው እያሉ ነው። ይህን የዘገበው '90 ሚኒት' ጋዜጣ ነው። ቼልሲ አላንድንና የዌስትሃሙን ዴክሌን ራይስ ለማስፈረም ሰባት ተጫዋቾቹን ሊሸጥ እንደሚችል ስካይ ስፖርት ዘግቧል። ባርክሌይ፣ አሎንሶ፣ ሩዲገር፣ ክሪስቴንሰን፣ ጆርጊንሆ፣ ድሪንክዎተርና ሞሰስ ለገበያ ሊቀርቡ እንደሚችሉ ተነግሯል። በሌላ በኩል ማንቸስተር ዩናይትድም አላንድን ማስፈረም ይፈልጋል። ነገር ግን የተጫዋቹ ወኪል የሆነው ሚኖ ራዮላ ከዩናትድ ጋር ያለው ግንኙነት ሰላማዊ ስላልሆነ ችግር ሊፈጥር ይችላል እየተባለ ነው ይላል ሚረር ባወጣው ዘገባ። ዩናይትድ አላንድን ማስፈረም ካልቻለ ፊቱን ወደ ኤቨርተኑን ዶሞኒክ ካልቨርት-ሌዊን ሊያዞር ይችላል። ሩዲገር፡ ቼልሲ ሊሸጣቸው ካሰባቸው ተጫዋቾች መካከል የሆነው ጀርመናዊው አንቶኒዮ ሩዲገር በፓሪስ ሴይንት ዠርሜይን ይፈለጋል። ይህን ያተመው የፈረንሳዩ 'ለ ፓሪዚያ' ነው። ሊቨርፑል፡ ቀያዮቹ የሪያል ማድሪዱን ብራዚላዊ ተከላካይ ኤደር ሚሊቶን ለማስፈረም አቅደዋል። አርጀንቲናዊው የ34 ዓመት ተጫዋች እዝቄል ጋሬይም በሊቨርፑሎች እየተፈለገ ነው። ይህን ዜና ያሰማው የስፔኑ ቶዶፊቻሄስ ነው። አርሴናል፡ የመድፈኞቹ አሠልጣኝ ማይክል አርቴታ የሪያል ማድሪዱን ብራዚላዊ አጥቂ ቪኒሺዬስ ጁኒዬርን ወደ ኤሜሬትስ ለማምጣት አቅደዋል። የ22 ዓመቱ አጥቂ ወደ ኤሜሬትስ በሚቀጥለው ጥር ወር በውሰት ሊመጣ ይችላል ተብሏል። አርቴታ ከወጣቱ አጥቂ በተጨማሪ የ28 ዓመቱን ስፔናዊ አማካይ ኢስኮ፤ ይፈልገዋል። ነገር ግን ተጫዋቹ ወደ ዩቬንቱስ መሄድን ይመርጣል - 'የደይሊ ስታር' እንደዘገበው። ባርሴሎና፡ የካታሎኑ ክለብ የአርሴናሉን ተከላካይ ሹከርዳን መስጣፊን ይፈልገዋል ይላል 'ስፖክስ' ጋዜጣ። የ28 ዓመቱ ሙስጣፊ ከአርሴናል ጋር ያለው ውል እየተገባደደ ነው። ጆንስ፡ የደርቢ ካውንቲ አሠልጣኝ የሆነው ዋይኒ ሩኒ የቀድሞ የቡድን አጋሩ ፊል ጆንስን ማስፈረም ይሻል። እንደ 'ሜትሮ' ዘገባ ከሆነ በማንቸስተር ዩናይትድ ቤት ዕድል ያጣው ጆንስ በዌስትብሮምም ይፈለጋል። የአውሮፓ እግር ኳስ የዝውውር መስኮት በሚቀጥለው የፈረንጆቹ ጥር ወር ይከፈታል። ማን ወደ የት ይሄዳል? ጊዜ ይፈታዋል።
|
https://www.bbc.com/amharic/news-55435608
|
business
|
ዓለምን ካስጨነቃት የዋጋ ንረት ተጠቃሚዎቹ እነማን ናቸው?
|
ከኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ተጽእኖ ሳያገግም የዩክሬን እና ሩሲያ ጦርነት የገጠመው የዓለም ምጣኔ ሃብት ከቀውስ አዙሪት ውስጥ አልወጣም። የነዳጅ እና የምግብ ምርቶች የዋጋ ንረት በመላው ዓለም በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕይወት ከባድ አድርጎታል። ታዲያ ዓለም በዋጋ ንረት በምትጨነቅበት በአሁኑ ወቅት በተለየ ሁኔታ ትርፍ እያጋበሱ ተጠቃሚ የሚሆኑ ዘርፎች አሉ። እነዚህ ከዋጋ ንረት የሚያተርፉ ድርጅቶች የትኞቹ ናቸው?
|
https://www.bbc.com/amharic/articles/crgj31l8mzzo
|
health
|
ኮሮናቫይረስ፡ በቫይረሱ የሞቱት የሮማኒያው ከንቲባ በምርጫ አሸነፉ
|
በኮሮናቫይረስ የሞቱት የሮማኒያው ከንቲባ በቅርቡ የተደረገውን ምርጫ በከፍተኛ ድምፅ አሸንፈዋል። 64 በመቶ የመራጮችንም ድምፅ ማግኘት ችለዋል። በደቡባዊቷ ሮማኒያ በምትገኘው ግዛት ዴቬሴሉ ከንቲባ የነበሩት ኢዮን አሊማን ለሶስተኛ ጊዜም አሸንፈዋል። ከሁለት ሳምንታት በፊት በመዲናዋ ቡካሬስት ህይወታቸው ያለፈው የቀድሞው ከንቲባ ስም ከተመራጮች ዝርዝር ውስጥ ነበር። የተመራጮች ዝርዝር ቀድሞ በመታተሙ ስማቸውን ማስወገድ እንዳልተቻለም ባለስልጣናቱ አስታውቀዋል። በዚህም ምክንያት የሞተ ሰው ከንቲባ ሆኖ እንደተመረጠም ተገልጿል። ሌላ ምርጫ እንደሚደረግም ባለስልጣናቱ ለሮይተርስ የተናገሩ ሲሆን በርካታ የግዛቲቷ ነዋሪዎች የቀድሞ ከንቲባቸውን ቀብር በመጎብኘት ሃዘናቸውን በመግለፅ ላይ ናቸው። በርካታ የመንደሪቷ ሰዎችም በመካነ መቃብሩ ተሰባስበው መታየታቸውን በማህበራዊ ሚዲያ የተጋሩ ቪዲዮዎች አሳይተዋል። "ይህ የአንተ ድል ነው" ሲል አንድ ግለሰብ ሲናገር ተሰምቷል። "እውነተኛ ከንቲባችን ነበር" በማለት ሌላ ግለሰብ ለአካባቢው የቴሌቪዥን ጣቢያ መናገሯን ሮይተርስ ዘግቧል። "ሁሉንም የግዛቲቷን ነዋሪ በእኩል አይን ያይ የነበረ፤ ህግንም ያከብር ነበር። እንደሱ አይነት ከንቲባ መቼም አይኖረንም" ግለሰቧ ማለቷንም ሮይተርስ አስነብቧል። የቀድሞ የባህር ኃይል አባል የነበሩት ኢዮን የግራ ክንፍ የሚያዘመው የሶሺያል ዲሞክራት ፓርቲ (ፒኤስዲ) አባል ነበሩ፤ በትናንትናው ዕለትም 57 አመታቸው ይሆን ነበር። በከንቲባነታቸው በህዝባቸው በከፍተኛ ሁኔታ መወደዳቸውም በፓርቲያቸው ዘንድ ጥሩ ስም አስገኝቶላቸዋል። ፓርቲያቸው በአሁኑ በተደረገው አገራዊ ምርጫ በተለያዩ ከተሞችና የምክር ቤቶች መቀመጫቸውን ለቀኝ ክንፍ አክራሪው ዩኤስ አር ፕላስ አሊያስና የአገሪቱን የመንግሥት ስልጣን በበላይነት ለተቆጣጠረው ሴንትሪስት ሊበራል አጥተዋል። በበርካታ የአውሮፓ ህብረት አባል አገራት የፍትህ ስርአቱ እንዲሻሻልና የሰፈነው ሙስና እንዲቆም የሚጠይቁ ከፍተኛ የተቃውሞ ሰልፎችን ተከትሎም ነው ፒኤስዲ በርካታ መቀመጫዎችን በፖርላመንት በድምፅ እንዲያጣ የተደረገው። የቀድሞ ከንቲባው ኢዮን ከሞቱ በኋላ በምርጫ ማሸነፍ በአገሪቷ የመጀመሪያው ክስተት አይደለም በጎሮጎሳውያኑ 2008 ኔኩላይ ኢቫስኩ የተባሉት ከንቲባም በጉበት በሽታ ከሞቱ በኋላ የቮይነስቲ ግዛት ከንቲባ ሆነዋል።
|
https://www.bbc.com/amharic/news-54336166
|
health
|
ኮሮናቫይረስ፡ አውሮፕላኖች እንዴት ነው በፀረ- ተህዋሲያን የሚፀዱት?
|
የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መከሰቱን ተከትሎ ቀጥ ብሎ የነበረውን የአለም የንግድ እንቅስቃሴን ለመመለስ በርካታ ጥረቶች እየተደረገ ነው። በተለያዩ አገራትም የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት ጥለዋቸው የነበሩ መመሪያዎችን እያላሉ ይገኛሉ። የወረርሽኝ ስርጭቱን ለመግታት አገራት አስተላልፈዋቸው ከነበሩ መመሪያዎች መካከል ዓለም አቀፍ በረራዎችን ማቆም፣ አየር ማረፊያዎቻቸውንና ድንበሮቻቸውን መዝጋት ይገኙበታል። በዚህም የተነሳ በርካታ የኢንዱስትሪ ዘርፎች በከፍተኛ ሁኔታ የተጎዱ ሲሆን በተለይም የአየር ትራንስፖርት ዘርፉ እንዲሽመደመድ ምክንያት ሆኗል። ከሰሞኑ አገራቱ ዘግተዋቸው የነበሩ ድንበሮቻቸውን ከፍተዋል፤ አለም አቀፍ አየር መንገዶቹም በረራዎችን ጀምረዋል። የአለም አቀፉ አቪየሽን ድርጅት የአየር ትራንስፖርቱ ዘርፍ እንዲያንሰራራና ተጓዦችም ደህንነታቸቸው በተጠበቀ መልኩ እንዲጓዙ ለማድረግ እንደ መመሪያነት የሚያገለግል አንድ ሰነድ አውጥቷል። በዚህም መመሪያ ውስጥ ከተካተቱት ጉዳዮች መካከል አውሮፕላኖች በምን መንገድ በፀረ- ተህዋሲያን መፀዳት እንዳለባቸውና የፅዳት ድግግሞሽንም ይመለከታል። እንዲሁ ከላይ ከላይ ሲታይ የአየር በረራና አካላዊ ርቀትን መጠበቅ የሚጣጣሙ አይመስሉም ። ነገር ግን ተቆጣጣሪ አካላት የተለያዩ ፕሮቶኮሎችን በማውጣት አስፈላጊ የሚባሉ የፅዳት መመሪያዎችን ለመተግበር ቀን ተሌት ደፋ ቀና በማለት ላይ ናቸው። ለአየር በረራዎች በዋነኝነት የሚያስፈልገው ፈጣንና፣ በቅልጥፍና የተሞላ ውጤታማ ፀረ- ተህዋሲያን የፅዳት ስርዓት መዘርጋት ነው። ከዚህም ጋር ተያይዞ ፍቃድ ያላቸው የፀረ- ተህዋሲያን ፅዳት በሚታዩና፣ ተደራሽ በሆኑ አካላት ላይ ጨርቅን እንዲሁም ተንቀሳቃሽ መርጫን በመጠቀም ማፅዳት ተግባራዊ እየተደረጉ ይገኛሉ። ነገር ግን ሁለቱም የማፅጃ መንገዶች በሰዎች አማካኝነት የሚካዱ ከመሆናቸው አንፃር ውጤታማነታቸውን የሚቀንስ ሲሆን መደረስ የማይችሉ የአውሮፕላኑ አካላትም ላይ ክፍተትን ይፈጥራሉ ተብሏል። ኦክስጅንና ኦዞን በሌላ መልኩ "አቶሚክ ኦክስጅንን" እንደ ፀረ-ተህዋሲያነት በመጠቅም አካባቢን ለማፅዳት ተጀምሯል። ከዚህም በተጨማሪ አምቡላንሶችን ለማፅዳት የሚጠቀሙበትን ፀረ ተህዋሲያንንም ለአውሮፕላን የውስጥ ክፍል ለማፅዳት እየታሰበበት ነው። ነገር ግን እነዚህ ማፅጃዎች ባላቸው የንጥረ ነገር በተለይም 'ኦክሳይድ' ባለው ባህርይ የኤሌክትሮኒክስ ቁሳቁሶች ላይ ጉዳት ሊፈጥሩ ይችሉ ይሆን በሚለው ስምምነት ላይ አልተደረሰም። መቶ በመቶ ውጤታማ የፀረ ተህዋሲያን ማፅጃ በሌለበት ሁኔታ ሌላኛው አማራጭ "የኦዞን" ንጥረ ነገሮችን መጠቀም ነው። በአሁኑ ወቅት ኦዞን በአውሮፕላን አካላት ላይ አገልግሎት ላይ ባይውልም በመጠጥ ቤቶችና በተለያዩ የንግድ ተቋማት ላይ በፀረ-ተህዋሲያን ማፅጃነት እያገለገለ ይገኛል። አካባቢውን የኦዞን ንጥረ ነገሮችን በመርጨት ውጤታማ የሆነ ፅዳትን ማግኘት ይቻላል። ነገር ግን ይህ ንጥረ ነገር በከፍተኛ መጠን ሲሆን ለሰዎች ጎጅ በመሆኑ ባለሙያን በመጠቀም መንገደኞች በሌሉበት ሁኔታ ሊረጭ ይገባል። ነገር ግን አሁንም ቢሆን ኦዞን ላይ ያለው ዋነኛ ጥያቄም የኦክሳይድ ንጥረ ነገር መጠኑ ነው፤ 'በአውሮፕላን የውስጥ አካልና የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ላይ ያለው ተፅእኖ ላይ መስማማት አልተቻለም። 'አየኖችና የአልትራቫዮሌት ጨረር ' በላብራቶሪ ውስጥ ተሞክሮ ውጤታማ የሆነው ከከባቢ አየር የሚለቀቀውን የውሃ ትነት ውስጥ የኦክስጅንና ሃይድሮጅን ንጥረ ነገሮችን ለይቶ በማውጣት ፀረ ተህዋሲያንን መፍጠር ነው። ይህ የፀረ ተህዋሲያን ማፅጃ መንገድ በጣም አድካሚና ለሁለት ሰዓታት ያህልም የሚወስድ ጊዜን ይፈጃል። ሆኖም ይሄ መንገድ በከፍተኛ ሁኔታ ውጤታማና መቶ በመቶ የሚተማመኑበት ነው። ከዚህም በተጨማሪ ፀረ ተህዋሲያኑ ቀላልና ተንቀሳቃሽ በሆነ መልኩ ትልልቅ የአውሮፕላን አካሎችን ማፅዳት ቢቻልም ለማፅዳት ግን ረዘም ያለ ጊዜ መውሰድ ያስፈልጋል። ሌላኛው ደግሞ ሲ የሚባለው የአልትራቫዮሌት ጨረር ሲሆን ይህ ጨረር ሳርስ የተባለውን የኮሮናቫይረስ አይነት ማጥፋት ይችላል። ለዚያም ነው ከፍተኛ ወጪ የሌላቸው ጨረሮች የአውሮፕላን አካላትን ለማፅዳት እየተነደፉ እንዲሁም እየተመረቱ ያሉት። ይህንም ተከትሎ በገበያው ላይ የነዚህ ጨረሮች ፍላጎት በመጨመሩ ምክንያት የአልትራቫዮሌት ጨረሮችን የሚያመርቱ ኩባንያዎች ምርታቸው በሚቀጥሉት አራት አመታት በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚጨምርም ግምታቸውን አስቀምጠዋል። በርካታ አማራጮች በርካታ የፀረ ተህዋሲያን ማፅጃ አማራጮች ከመኖራቸው አንፃር በተለያየ ሂደትም ላይ ናቸው። አሁንም ቢሆን የትኛው የበለጠ ተስማሚ እንደሆነም እስካሁንም አይታወቅም። የትኛው የፀረ ተህዋሲያን ስርአት የበለጠ ውጤታማ እንደሚሆን መለየት ከተቻለ በኋላ ምን ያህል ጊዜም ይወስዳል የሚለውን ማየት አስፈላጊ እንደሆነም እየተነገረ ነው። የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ አሁንም ስጋት ሆኖ ባለበት ወቅት በርካታ አየር መንገዶች በረራ መጀመራቸው ጋር ተያይዞ ቫይረሱ እንዳይሰራጭ የማድረግ ከፍተኛ ኃላፊነትና ሸክም ተጥሏባቸዋል። የአውሮፕላኑ ሰራተኞች፣ መንገደኞችን ደህንነት በሚያስጠብቅ መልኩ አውሮፕላኖቹ በፀረ ተህዋሲያን መፀዳትም ግዴታ ነው። እነዚህ የፀረ ተህዋሲያን ማፅጃ ዘዴዎች ቫይረሱን መግታት ብቻ ሳይሆን የአየር መንገድ ኃላፊዎችም ሆነ ተቆጣጣሪዎች የሚያስወጣቸውን ዋጋና እንዲሁም ቀልጣፋና ውጤታማ በሆነ መንገድ መፅዳት የሚችሉበትን ሁኔታ መገምገም ይጠበቅባቸዋል። በአንድ መልኩ የአየር ትራንስፖርቱ ወደቀደመ ሁኔታ እንዲመለሱ ግፊት እያደረጉ ሲሆን በሌላ መልኩ በዚህ ወረርሽኝ መካከል የተጓዦች ደህንነት በተጠበቀ መልኩ አገልግሎታቸውን መመለስና በወረርሽኙ ምክንያት ያጡትን ገቢ ለማግኘትም አጣጥመው መሄድ ይጠበቅባቸዋል። በተለይም አውሮፕላኖቹ የሚፀዱበትን ደረጃና ያለውን የስጋት መጠንን መቀነስና፤ የሚፀዳበትን ጊዜ አጣጥመው መሄድም ይጠበቅባቸዋል። የመንገደኞችን ጤንትና ደህንነት ቅድሚያ በመስጠትም አየር መንገዶቹ እነዚህን ተግባራት እንዲያከናውኑም አለም አቀፉ አቪየሽንም መመሪያ ሰጥቷል። ከአለም አቀፉ አቪየሽን ቡድንና፣ የትራንስፖርት ዘርፍ ተመራማሪዎች የተውጣጡ ግለሰቦችም ውጤታማ የሆኑትን የፀረ ተህዋሲያን የማፅጃ ዘዴዎችንም ለመቀየስ ከፍተኛ ምርምሮችን እያደረጉም ነው፤ የተለያዩ መመሪያዎችንም በማውጣትም ላይ ይገኛሉ።
|
https://www.bbc.com/amharic/53627279
|
politics
|
ቤኒቶ ሙሶሊኒ ላይ የተኮሰችው አየርላንዳዊት
|
ጊዜው በፈረንጆቹ ሚያዝያ 7 1926 ነበር። ቦታው ደግሞ የጣልያኗ መዲና ሮም። የሃገሬው ሰው በ20ኛው ክፍለ ዘመን ከነበሩ ኃያላን መካከል አንዱ የነበረውን ግለሰብ ለማየት ተኮልኩሏል። አንዲት አየርላንዳዊት ሴት ግን በሰውዬው ወሬ ብዙም አልተማረከችም። ዓላማዋ ሌላ ነበር። ድንገት የተኩስ ድምፅ ተሰማ። ሰው ወዲያ ወዲህ ተበታተነ። ለተሰበሰበው ሰው መልዕክቱን ሲያስተላልፍ የነበረው ቤኒቶ ሙሴሊኒም ወደኋላ ተዘረጋ። ጥይቷ የፈለቀችው ከአየርላንዳዊቷ ሴት አፈሙዝ ነበር። ዒላማዋን አልሳተችም። የሙሶሊኒን አፍንጫ ቦረሸችው። ሙሶሊኒ ግን አልሞተም። የጣልያኑ መሪ ከተቃጣበት የግድያ ሙከራ መትረፍ ቻለ። አውሮፓውያን በ20ኛው ክፍለ ዘመን ፋሺስታዊነትን ለመከላከል ከፈፀሟቸው ድርጊቶች መካከል የቫዮሌት ጊብሰን ድርጊት ሁሌም ይነሳል። ሙሶሊኒን ለመግደል ጥረት ካደረጉ አራት ሰዎች መካከል የተሻለ ሙከራ ያደረገችው እሷ ናት። አየርላንዳዊቷ ሙሶሊኒን ለመግደል ሙከራ ካደረገች እነሆ መቶ ዓመት ሊደፍን ጥቂት ዓመታት ይቀሩታል። ይህን ለማሰብ ደብሊን ውስጥ መታሰቢያ እንዲቆምላት ሥራዎች ተጀምረዋል። ቫዮሌት ሙሶሊኒ ላይ ሶስት ጥይቶች ተኩሳለች። አራተኛውን ልትለቀው ስትል ግን ሽጉጧ ነከሰ። ይሄኔ የሙሶሊኒ ጠባቂዎች የከበቧት። የከተማዋ ፖሊስ ጣልቃ ገብቶ በቁጥጥር ሥር ባያውሏት ኖሮ የጠባቂዎቹ ጡጫ ሲሳይ ትሆን ነበር። ጣልያን ውስጥ ታሥራ ከቆች በኋላ ወደ እንግሊዝ እንድትሄድ ተደረገ። ይህ የሆነው ጣልያን ውስጥ የፍርድ ሂደቱ ቢካሄድ ውርደት ይሆናል በሚል ነው ይባላል። ቫዮሌት እንግሊዝ ውስጥ ባለው የቅዱስ አንድሩ የአእምሮ ሕሙማን መታከሚያ ማዕከል ገብታ በስተመጨረሻ በፈረንጆቹ 1956 ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች። ከእንግሊዛዊ አየርላንዳዊ ከበርቴ ቤተሰብ የተወለደችው ቫዮሌት ክዊን ቪክቶሪያ ውስጥ ነበር የምትኖረው። አሁን የደብሊን ከተማ በስሟ መታሰቢያ እንዲቆም ረቂቅ አፅድቆ ወደ ሥራ ገብቷል። የከተማዋ አስተዳደር የሴትዬዋ ድርጊት በታሪክ መዝገብ ብዙም ባለመዘገቡ የሠራችውን 'ፀረ-ፋሺስት' ሥራ የሚዘክር መታሰቢያ ሊቆምላት ይገባል ብሏል። "የብሪታኒያ መንግሥትና ቤተሰቦቿ የሷን ድርጊት እንደ 'እብድ ሰው' ተግባር ሳይሆን እንደ ፖለቲካ ሊያዩት ይገባል" ይላል ረቂቁ። በጀግንነቷ ምክንያት የተሰቃየችው ረቂቁን ለደብሊን ከተማ ምክር ቤት ያቀረቡት ገለልተኛው የከተማው ምክር ቤት አባል ማኒክስ ፍሊን "ቫዮሌት ጊብሰን በአየርላንድና እንግሊዝ መንግሥታት የተረሳች ናት" ሲሉ ይከራከራሉ። "ልክ እንደበርካታ ሴቶች እጅግ ድፍረት የተሞላበት ድርጊት ብትፈፅምም ተገፍታለች" ሲሉ ለቢቢሲ ሰሜን አየርላንድ ጣቢያ ይናገራሉ። "ቫዮሌት ጊብሰን የሠራችው ሥራ የሚያሳፍር ነው' 'እብድ ናት' በማለት እንድትደበቅ ተደርጋለች።" የቫዮሌት ቤተሰቦች ለመታሠቢያ ኃውልቱ ፈቀድ ሰጥተዋል። በሚቀጥሉት ሳምንታትም ረቂቁ ፀድቆ ወደ ሥራ እንደሚገባ ይጠበቃል። መታሰቢያ በልጅነቷ ያደገችበት ደብሊን ውስጥ የሚገኘው የሜሪዬን አደባባይ እንዲሆንም ሐሳብ ቀርቧል። ደብዳቤ ለቸርችል የቫዮሌት ታሪክ ወደ አደባባይ ብቅ ያለው በፈረንጆቹ 2014 አርቲኢ የተሰኘው ራድዮ ጣቢያ በሠራው ዘጋቢ ቅንብር ምክንያት ነው። ዘገባው 'ሙሶሊኒ ላይ የተኮሰችው ሴት' ከተሰኘው መፅሐፍ ላይ የተወሰደ ነው። ታሪኳ ላይ እንደተመዘገበው ቫዮሌት ከቅዱስ አንድሩ ሆስፒታል እንድትለቀቅ በወቅቱ ለነበሩ ኃያላን መሪዎች ደብዳቤ ፅፋ ነበር። ከእነዚህ መካከል የአሁኗ የእንግሊዝ ንግሥት ኤሊዛቤት ይገኙበታል። ሌላኛው ደብዳቤ የተላከው በወቅቱ የእንግሊዝ መሪ ለነበሩት ዊንስተን ቸርችል ነበር። ቸርችል በደብሊን ከተማ ባደጉ ወቅት ከቫዮሌት ጋር እውቅና ሳይኖራቸው አይቀርም ይላል ታሪኳን የሚዘግበው መፅሐፍ። ለዊንስተን ቸርችል የተፃፈው ደብዳቤ አሁንም አለ። ነገር ግን በወቅቱ ደብዳቤው ለቸርችል ሊደርስ አልቻለም። የራድዮ ዘገባው አዘጋጆች ወደ ጣልያን ሄደው በሠሩት ጥናት መሠረት ሙሶሊኒ ላይ ከተሞከሩ ግድያዎች መካከል ብዙ መረጃ የተሰበሰበው በቫዮሌት ዙሪያ ነው። "ይህን ድርጊት የፈፀመው ወንድ ቢሆን ኖሮ ይሄን ሃውልት ወይም ሌላ መታሰቢያ ተሠርቶለት ነበር። እሷ ሴት ስለነበረች ታሠረች። እኛ ታሪኩን ለሕዝብ ይፋ በማድረጋችን ደስተኞች ነን" ይላሉ የዘገባው አዘጋጆች። ቤኒቶ ሙሶሊኒ ማነው? የሙሶሊኒ ብሔራዊ ፋሺስት ፓርቲ ጣልያን ውስጥ ወደ ሥልጣን የመጣው ከአንደኛው ዓለም ጦርነት በኋላ ነው። 'ብላክሸርትስ' በተሰኙ ታጣቂዎች የሚደገፈው ፖርቲ ተቀናቃኞችን በኃይል ያስፈራራ ነበር። ፋሺስቱ ፓርቲ በ1920ዎቹ ሥልጣን ከያዘ በኋላ ዴሞክራሲያዊ የሚባሉ ተቋማትን አፈራረሰ። ሙሶሊኒ የጣልያን አምባገነናዊ መሪ ሆነው የተሾሙት በፈረንጆቹ 1925 ነበር። ሙሶሊኒ በስፔን የእርስ በርስ ጦርነት ወቅት የጁኔራል ፍራንቺስኮ ፍራንኮ ደጋፊ ነበር። በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ደግሞ የአዶልፍ ሂትለር ቀኝ እጅ ነበር። ሙሶሊኒ የሂትለርን አንዳንድ ፖሊሲዎች ወስዶ በ1938 የጣልያኑ አይሁዳዊያን ሙሉ በሙሉ መብታቸው እንዲገፈፍ አድርጎ ነበር። በአይሁዶች ጅምላ ጭፍጨፋ [ሆሎኮስት] ወቅት ከ7 ሺህ 500 በላይ የጣልያን አይሁዶች እንደተገደሉ ይታመናል። ኢትዮጵያ በጣልያን ለሁለተኛ ጊዜ የተወረረችው በሙሶሊኒ አምባገነናዊ ሥርዓት ወቅት ነበር። ሙሶሊኒ ከምዕራባዊያን ጦር ለማምለጥ ሲሞክር በጣሊያን ነፃ አውጭዎች ተይዞ የተገደለው በፈረንጆቹ 1945 ነው።
|
https://www.bbc.com/amharic/news-56145284
|
business
|
ኮሮናቫይረስና የነዳጅ ዘይት ምን አገናኛቸው?
|
ኮሮናቫይረስ የማይነካው ነገር እንደሌለ እየታየ ነው። በየሰበብ አስባቡ እያሻቀበ የነበረውን ነዳጅ ዘይትን ሊነካው ዳርዳር እያለ ነው። በሽታው አሳሳቢ ደረጃ ላይ በደረሰበት በአሁኑ ጊዜ የዓለማችን ትልልቆቹ የነዳጅ አምራች አገራት በሽታው ካስከተለው ችግር ለመቋቋም በሚያደርጉት ጥረት ውስጥ ምርታቸው ሊቀንስ ይችላል እየተባለ ነው። የነዳጅ ዋጋን ለመደገፍ እርምጃ እንዲወሰድ እየተጠየቀ ባለበት በአሁኑ ወቅት የነዳጅ አምራች አገራት ማህበር የሆነው ኦፔክ እና አጋሮቹ በዚህ ሳምንት ስብሰባ እንደሚቀመጡ እየተጠበቀ ነው። • ኮሮናቫይረስ፡ ኢትዮጵያዊያን ተማሪዎች በቻይና • አባቱ በኮሮናቫይረስ የተጠረጠረው አካል ጉዳተኛ ታዳጊ ሞተ በጥር ወር መጀመሪያ ላይ የነዳጅ ዋጋ በዓመት ውስጥ ከታየው ከፍ ብሎ በ20 በመቶ ካሻቀበ በኋላ አሽቆልቁሎ ዝቅተኛው ዋጋው ላይ ይገኛል። ስለምን ይህ የቫይረስ ወረርሽኝ እንዲህ ያለው ከፍተኛ ተጽእኖን በዓለም አቀፉ የኃይል ገበያ ላይ ሊያስከትል ቻለ? የቻይናዊያን አዲስ ዓመት የበዓል ጊዜ በአብዛኛው የአገሪቱ ክፍል በበሽታው ምክንያት በመራዘሙና የጉዞ እገዳ በመደረጉ ፋብሪካዎች፣ ቢሮዎችና መደብሮች ዝግ ሆነው ይገኛሉ። ይህም ማለት አስከ 14 ሚሊዮን በርሜሎችን በቀን ውስጥ የምትጠቀመውና የዓለማችን ትልቋ የድፍድፍ ነዳጅ ገዢ አገር የሆነችው ቻይና ማሽኖቿን ለማንቀሳቀስ፣ ለተሽከርካሪዎችና ለኤሌክትሪክ ኃይል ወትሮ ከምትፈልገው ነዳጅ ዘይት በእጅጉ የቀነሰውን እንድትጠቀም አድርጓታል። በወረርሽኙ ምክንያት በርካታ አየር መንገዶች ወደ ቻይና የሚያደርጓቸውን በረራዎች በማቋረጣቸው የተነሳና በቻይና ውስጥ ባለው የጉዞ እገዳ ሳቢያ በረራዎች በመቀነሳቸው ለአውሮፕላን ነዳጅ ያለው ፍላጎት በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሰዋል ተብሎ ይታሰባል። • ኮሮናቫይረስ፡ ምን ያህል አሳሳቢ ነው? • ካሜሮናዊው በኮሮናቫይረስ በመያዝ የመጀመሪያው አፍሪካዊ ሆነ ብሉምበርግ በዚህ ሳምንት እንደዘገበው የቻይና ዕለታዊ የድፍድፍ ነዳጅ ፍጆታ በ20 በመቶ ቀንሷል። ይህም ማለት ብሪታኒያና ጣሊያን በአንድ ላይ በቀን የሚያስፈልጋቸውን ነው። በዚህም ሳቢያ በቻይና መንግሥት የሚተዳደረው የእስያ አህጉር ትልቁ የነዳጅ ማጣሪያ ሲኖፔክ በየቀኑ የሚያጣራውን የድፍድፍ ነዳጅ መጠን በ600 ሺህ በርሜሎች ቀንሷል። ይህም ከሥራው 12 በመቶው አቁሟል ማለት ሲሆን ከ10 ዓመታት በላይ ባለው ጊዜ ውስጥ ከፍተኛው ቅናሽ ነው። በነዳጅ ዘይት ላይ የታየው ከፍተኛ ቅናሽ የኃይል ኢንዱስትሪውን በከፍተኛ ደረጃ እንዳሳሰበው የዘርፉ ባለሙያዎች እየተናገሩ ነው። በነዳጅ ፍላጎት ላይ የተከሰተው ከፍተኛ ቅናሽ በቻይና ውስጥ የተከሰተውን የሥራ መቀዛቀዝን የሚያሳይ ግልጽ ምልክት ነው። በተጨማሪም ባለፉት 30 ዓመታት ውስጥ ቻይናን ካጋጠማት የኢኮኖሚ ዕድገት መቀነስ ክስተት ውስጥ ዝቅተኛው ማጋጠሙ ደግሞ የነዳጅ ፍጆታዋን የበለጠ ይቀንሰዋል ተብሏል። የተባሉት በቻይና የሳይንስ አካዳሚ ውስጥ ተመራማሪ የሆኑነት ዣንግ ሚንግ እንደሚሉት የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ በዓመቱ መጀመሪያ ላይ ባሉት ሦስት ወራት የአገሪቱን ዓመታዊ የኢኮኖሚ ዕድገት ከ5 በመቶ በታች ሊያወርደው ይችላል። • "ኮሮናቫይረስ በአሜሪካ የሥራ ዕድልን ሊያሳድግ ይችላል" ያደጉት አገራት እድገታቸውን ለማጠናከር ትግል በሚያደርጉበት ጊዜ ቻይና የዓለማችን ሁለተኛዋ ግዙፍ ኢኮኖሚና ለዓለም የኢኮኖሚ ዕድገት አንቀሳቃሽ ሞተር ናት። የዓለም ገንዘብ ድርጅት ዳይሬክተር የሆኑት ክሪስታሊና ጆርጂዮቫ ባዚህ ሳምንት እንዳሉት ወረርሽኙ ቢያንስ ለአጭር ጊዜ የዓለም ኢኮኖሚ ዕድገትን ያቀዛቅዘዋል፤ ነገር ግን የወደፊቱን ለመናገር አሁን ጊዜው ገና እንደሆነም አመልክተዋል። እያሽቆለቆለ ያለውን የነዳጅ ዋጋ ለማሳደግ ታላላቆቹ የዓለም ነዳጅ ዘይት አምራቾች ለገበያ የሚያቀርቡትን ምርት በከፍተኛ መጠን ለመቀነስ በሚያደርጉት ስብሰባ ላይ እንደሚወያዩ እየተነገረ ነው። የኮሮናቫይረስ ክስተት ለነዳጅ የለውን ፍላጎት እንዲቀንስ በማድረጉ ምክንያት የነዳጅ አምራችና ላኪ አገራት ማኅበር የሆነው ኦፔክ አባል የሆነችው ኢራን ሰኞ ዕለት እየወደቀ ያለውን የነዳጅ ዋጋ ለመደገፍ እርምጃዎች እንዲወሰዱ በይፋ ጠይቃለች። የኦፔክ አባል አገራትና ሩሲያ በዚህ ሳምንት ያደርጉታል ተብሎ በሚጠበቀው ስብሰባ ላይ በቀን ለገበያ ከሚያርቡት የነዳጅ ምርት ከ500 ሺህ እስከ 1 ሚሊዮን በርሜል የሚደርሰውን ለመቀነስ ይወያያሉ ተብሏል።
|
https://www.bbc.com/amharic/news-51368390
|
sports
|
በርካታ ኢትዮጵያውያን የሚጠበቁበት የቤልግሬዱ የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና
|
ሰርቢያ ቤልግሬድ ውስጥ ዛሬ ከመጋቢት 9 ተጀምሮ አስከ 11/2014 ዓ.ም በሚቆየው የዓለም የቤት ውስጥ የአትሌቲክስ ሻምፒዮና አፍሪካዊያን አትሌቶች ሜዳሊያ ያገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል። ኬንያዊው አትሌት ፈርዲናንድ ኦሙርዋ ኦማንያላ ከእነዚህ መካከል አንዱ ሲሆን የዩሴይን ቦልትን የ100 ሜትር የዓለም ክብረወሰን መስበር እንደሚችል ተናግሯል። ኬንያዊው አትሌት በሰርቢያው ሻምፒዮና ውድድሩን 60 ሜትር ይጀምራል። የ26 ዓመቱ አትሌት በ9.77 በሆነ ሰከንድ የአፍሪካን የ100 ሜትር ክብረወሰን በእጁ አስገብቷል። በአጭር ርቀት መሻሻል ካሳየ የቦልትን ክብረ ወሰን (9.58 ሰከንድ) ለመስበር እንደሚረዳው ያምናል። "ምንም የማይቻል ነገር የለም ብዬ አምናለሁ። የዓለም ክብረ ወሰን የሚሳካ ነገር ነው" ሲል ኦማንያላ ለቢቢሲ ስፖርት አፍሪካ ተናግሯል። "ይህን ክብረ ወሰን መስበር የሚችል ሰው ካለ እኔ ነኝ ብዬ አምናለሁ።'' "የአፍሪካን ክብረ ወሰን ተመልከቱ። ሩጫ ስጀምር ሰዎች በቅርቡ አይሰበርም ብለው አስበው ነበር። ይህን ግን ባለፈው ዓመት አሳክቻለሁ።'' ይህም የኦማንያላ ክብረወሰን የምንጊዜም ፈታኝ ሰዓቶች ስምንተኛው አድርጎታል። ይህን ግን ያሳካው የ14 ወራት የአበረታች መድኃኒት እገዳ በ2017 ከተጣለበት በኋላ ነው። መድኃኒቱ የተገኘበት በውስጡ ስቴሮይድ አለበት ያለውን የህመም ማስታገሻ ከወሰደ በኋላ መሆኑን ጠቅሶ "በሁኔታው ተጎድቻለሁ" ብሏል። ሻምፒዮን ለመሆን ጣሊያናዊውን የ100 ሜትር የኦሊምፒክ ሻምፒዮን ማርሴል ጃኮብስን እና የወቅቱን የቤት ውስጥ ሻምፒዮን አሜሪካዊውን ክርስቲያን ኮልማንን ማሸነፍ ይኖርበታል። በቤልግሬድ የሚወዳደሩ ሌሎች አፍሪካውያንስ? በ2022ቱ የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ከ137 አገራት የተውጣጡ 680 አትሌቶች ይሳተፋሉ። ውድድሩ ከመጋቢት 9 እስከ 11/2014 ሰርኒያ ቤልግሬድ ውስጥ ይካሄዳል። ስድስቱ ተጠባቂ አፍሪካዊያን ሰለሞን ባረጋ (ኢትዮጵያ) - የ22 ዓመቱ አትሌት የ10,000 ሜትር የኦሊምፒክ ሻምፒዮን ነው። በ2018 በዓለም የቤት ውስጥ ውድድር በ3000 ሜትር ያገኘውን የብር ሜዳሊያ ለማሻሻል ይወዳደራል። ለሜቻ ግርማ (ኢትዮጵያ) - በ3000 ሜትር መሰናክል የዓለም እና የኦሊምፒክ የብር ሜዳሊያ አሸናፊ ነው። የ21 ዓመቱ አትሌት የ3000 ሜትር አሸናፊ ለመሆን ከሰለሞን ጋር ይፎካከራል። ሳሙኤል ተፈራ (ኢትዮጵያ) - የ1500ሜ የዓለም የቤት ውስጥ ክብረ ወሰን ባለቤት ሲሆን በ2018 በርሚንግሃም ላይ ያገኘውን የወርቅ ሜዳሊያ ለማስጠበቅ ይወዳደራል። ጉዳፍ ፀጋይ (ኢትዮጵያ) - የ5,000 ሜትር የኦሊምፒክ እና የ1500 ሜትር የዓለም ሻምፒዮና የነሐስ ሜዳሊያ አሸናፊዋ 24 ዓመቷ አትሌት በ1500 ሜትር ትጠበቃለች። ኢሴ ብሩሜ (ናይጄሪያ) - የኦሊምፒክ እና የዓለም ሻምፒዮና የነሐስ ሜዳሊያ አሸናፊዋ የ26 ዓመቷ አትሌት፣ የአፍሪካ ሻምፒዮን ናት። በሴቶች የአግድሞሽ ዝላይ ውድድር ትሳተፋለች። ሃሊማ ናካዪ (ኡጋንዳ) - የ27 ዓመቷ አትሌት በ2019 ዶሃ ላይ ባስመዘገበችው የ800 ሜትር የዓለም ሻምፒዮና ወርቅ ላይ ተጨማሪ ድል ለማስመዝገብ ትፎካከራለች። ያሲር ትሪኪ (አልጄሪያ) - ባለሦስትዮሽ ዝላይ (ትሪፕል ጃምፕ) በ16.95 ሜትር በመዝለል ከወቅቱ የዓለም ምርጥ 5ቱ ውስጥ ተካቷል።
|
https://www.bbc.com/amharic/news-60788088
|
politics
|
ምርጫ 2013፡ የምርጫ ውጤት በምርጫ ክልል ደረጃ ረቡዕና ሐሙስ ይገለጻል ተባለ
|
ሰኞ ዕለት የተካሄደው ምርጫ ውጤት በምርጫ ክልል ደረጃ ረቡዕና ሐሙስ ይፋ እንደሚደረግ የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ አስታወቀ። ቆጠራ በተጠናቀቀባቸው ምርጫ ጣቢዎች ውጤቶች ከማክሰኞ ንጋት ጀምሮ ይፋ ሲደረጉ የቆዩ ሲሆን፤ የምርጫ ጣቢያ ውጤቶች ወደ ምርጫ ክልሎች ከተላኩ በኋላ "ነገ [ረቡእ] እና ከነገ ወዲያ [ሐሙስ] የምርጫ ክልል ውጤት ይፋ ይደረጋል" ሲሉ የቦርዱ የኮምዩኒኬሽን አማካሪ ሶሊያና ሽመልስ ተናግረዋል። የምርጫ ክልል ውጤቶች ደግሞ ከመላው አገሪቱ ወደ ማዕከል ገብተው አስፈላጊው ማጣራት ከተካሄደ በኋላ ቦርዱ አጠቃላይ ውጤቱን ይፋ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማክሰኞ ከሰዓት በበኋላ በሰጠው መግለጫ እስከ ቀጣይ 10 ቀናት ድረስ ቢያንስ ጊዜያዊ የሆነ የአጠቃላይ የምርጫ ውጤት ይፋ አድርጋለሁ ብሏል። ከዚህ ባሻገር የተለያዩ ግለሰቦች የምርጫ ጣቢያ ውጤቶችን በመያዝ የመጨረሻ ውጤት በማስመሰል ይፋ ከማድረግ ተግራባቸው እንዲቆጠቡ ቦርዱ ጠይቋል። የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ኮምዩኒኬሽን አማካሪ ሶሊያና ሽመልስ በርካታ አክቲቪስቶች እና ማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ከአንድ ምርጫ ጣቢያ የተገኘ ውጤን መሠረት በማድረግ 'የዚህ ምርጫ ክልል አሸናፊ እከሌ ነው' እያሉ ሲውጁ ተመልክተናል ብለዋል። የምርጫ ውጤቶችን ይፋ ማድረግ የሚችለው ምርጫ ቦርድ ብቻ መሆኑን ያስታወሱት ሶሊያና፤ መሰል ተግባራት "ተቀባይነት የሌለው እና ወንጀል ጭምር ነው" ብለዋል። ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምን ያክል ሰዎች ድምጽ ለመስጥት ወጡ የሚለው አሃዝ እስካሁን እንደሌለው በመጥቀስ በርካታ ቁጥር ያለው ሰው ግን ድምጽ ለመስጥ መውጣቱን መገንዘቡ ተገልጿል። "በከተማም በገጠርም በርካታ ሕዝብ ድምጽ ለመስጥት ወጥቷል። ይህም በጣም አስደሳች ነበር" ብለዋል የቦርዱ የኮምዩኒኬሽን አማካሪ ሶሊያና ሽመልስ። ሰኞ ሰኔ 14/2013 ዓ.ም በአብዛኛው የአገሪቱ ክፍሎች በተካሄደው ምርጫ የተሰጡትን ድምጾች በመቁጠር ከማክሰኞ ጠዋት ጀምሮ በምርጫ ጣቢያ ደረጃ ውጤቶች ይፋ እየተደረጉ ሲሆን በበርካታ ቦታዎች ውጤቶች ታውቀዋል። ከዚህ ባሻገር በተለያዩ አካባቢዎች ባጋጠሙ መስተጓጎሎች ሰኞ ዕለት ድምጽ ሳይሰጥባቸው በቀሩ አካባቢዎች ዛሬ ማክሰኞ ዕለት መራጮች ድምጽ ሰሰጡ ውለዋል። ከምርጫው ጋር በተያያዘ ወደ ኢትዮጵያ ከገቡ በኋላ በሆቴል ክፍላቸው ውስጥ ሕይወታቸው አልፎ ስለተገኙት አሜሪካዊ ግለሰብን በተመለከተም ቦርዱ ክስተቱን ከፖሊስ መስማቱን ተናግረዋል። "ግለሰቡ በሆቴል ክፍላቸው ሕይወታቸው አልፎ መገኘቱን ሰምተናል። ሆቴል ክፍላቸው ወድቀው ነው የተገኙት። እጅግ አሳዛኝ አጋጣሚ ነው" ካሉ በኋላ የግለሰቡ አሟሟት ከምርጫው ጋር የተገናኘ አለመሆኑን ተናግረዋል። ሶሊያና ግለሰቡ ዓለም አቀፍ የምርጫ ታዛቢ አለመሆናቸውን ጠቅሰው በእንግድነት ከምርጫ ቦርድ ባጅ ወስደው እንደነበረ ተናግረዋል። "የመታዘብ ሥራን የሚሰሩ አልነበሩም። ለእንግዶች የሚሰጥ ባጅ ነው የወሰዱት። ከካርተር ሴንተር ለመታዘብ የመጣ የለም" ብለዋል። ባለፈው ዓመት ሊካሄድ ታስቦ በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ወደዚህ ዓመት ተሸጋግሮ በሁለት ዙሮች ምርጫው እንዲካሄድ በተወሰነው መሰረት የመጀመሪያው ዙር ምርጫ ሰኞ ሰኔ 14/2013 ዓ.ም ተካሂዷል። ሁለተኛው ዙር ምርጫ በሶማሌና በሐረሪ ክልሎች እንዲሁም በሌሎች አንዳንድ አካባቢዎች ከሁለት ወራት በኋላ ጳጉሜ 01/2013 ዓ.ም ይካሄዳል።
|
https://www.bbc.com/amharic/news-57554222
|
health
|
በኒው ዚላንድ ሰዎች በፍቃዳቸው እንዲሞቱ የሚደነግግ ሕግ ሊወጣ ነው
|
በኒው ዚላንድ በጠና የታመሙ ሰዎች በፍቃዳቸው እንዲሞቱ የሚደነግግ ሕግ ሊወጣ ነው። ባለፈው ወር በተካሄደ ሕዝበ ውሳኔ 65.2% መራጮች የፍቃድ ሞትን ደግፈዋል። ዩትኔዝያ ወይም የፈቃድ ሞት በጠና የታመሙ ወይም ከስድስት ወር በላይ እንደማይኖሩ የተነገራቸው ሰዎች በህክምና እርዳታ ሕይወታቸው እንዲያልፍ የሚደረግበት ሂደት ነው። ሕጉ በቀጣዩ ዓመት ጥቅምት ወር ጸድቆ ይተገበራል ተብሎ ይጠበቃል። ኒው ዚላንድ ሕጉን ካጸደቀች የፈቃድ ሞት ከሚተገበርባቸው ጥቂት አገሮች አንዷ ትሆናለች። ዩትኔዝያ ከተፈቀደባቸው አገሮች ኔዘርላንድ እና ካናዳ ይጠቀሳሉ። ኒው ዚላንዳውያን ባለፈው ወር መሪያቸውን ሲመርጡ ስለ ፈቃድ ሞት እና ዕጸ ፋርስ ሕዝበ ውሳኔ አድርገዋል። ዕጸ ፋርስን ለመዝናኛ መጠቀም ሕጋዊ እንዲሆን ድምጽ የሰጡት 46.1% ብቻ ሲሆኑ፤ 53.1% ተቃውመዋል። የፈቃድ ሞትን ጠቅላይ ሚንስትር ጀሲንዳ አርደን እንዲሁም ተቀናቃኛቸው ጁዲት ኮሊንስም ይደግፉታል። ሕዝቡም ሕጋዊ ይሁን ብሎ እንደሚመርጥ ይጠበቅ ነበር። ባለቤቱ የሞተችበት ማት ቪከርስ "ርህራሄ እና ደግነት አሸንፈዋል። በጠና የታመሙ ኒው ዚላንዳውያን ሕይወታቸውን ማሳለፍ ስለሚችሉ ደስ ብሎኛል" ሲል የተሰማውን ገልጿል። ጠበቃ የነበረችው ባለቤቱ የአንጎል እጢ ሲገኝባት በፈቃዷ ለመሞት ክስ ብትመሠረትም ሳታሸንፍ በጠና ታማ ከአምስት ዓመታት በፊት ሞታለች። "ባለቤቴ መሞት አትሻም ነበር። ማንም ሰው መሞት አይፈልግም። ነገር ግን መኖር የምርጫ ጉዳይ ነው። ስቃይ እየበረታ ሲሄድ መሞት አንዱ ምርጫ መሆን አለበት" ብሏል። አንድ ሰው በፈቃዱ ለመሞት በጠና የታመመ ወይም ከስድስት ወር በላይ እንደማይኖር የተረጋገጠ መሆን አለበት። ሰውነቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተዳከመ እንደሄደና ውሳኔው ላይ ለመድረስ በቂ መረጃ እንዳለው ማረጋገጥም ተገቢ ነው። ሂደቱ የሚመራው በዶክተር ወይም በነርስ ነው። አንድ ሰው እድሜው ስለገፋ፣ የአእምሮ ህመም ስላለበት ወይም የአካል ጉዳት ስላለበት የፍቃድ ሞት ሕግን መተግበር አይችልም። ሕጉን የሚቃወሙ ሰዎች "እንድንኖር እንጂ እንድንሞት አትርዱን" ሲሉ ምክር ቤት ሄደው ተቃውሞ አሰምተዋል። ሕጉ ለማኅበረሰቡ አስጊ እንደሆነ እና ራስን ማጥፋትን ለመግታት ከወጣ መርህ ጋር እንደሚቃረን ይናገራሉ። ሌላው መከራከሪያ ነጥብ በጠና የታመሙ ሰዎች የቤተሰብ ሸክም ላለመሆን ብለው በፈቃዳቸው ሊሞቱ ይችላሉ የሚለው ነው። ዩትኔዝያን አጥብቆ ሲተች የነበረ ቡድን "የኒው ዚላንድ ዜጎች የተሳሳተ ሕግ እንዲጸድቅ ድምጽ በመስጠታቸው አዝነናል" ሲል መግለጫ አውጥቷል። የፈቃድ ሞትን ሕጋዊ ያደረጉ አገሮች የኒው ዚላንድን ሕዝበ ውሳኔ በቅርበት ሲከታተሉ ነበር። ከነዚህ መካከል ቤልጄም፣ ካናዳ፣ ኮሎምቢያ፣ ሉግዘምበርግ እና ኔዘርላንድስ ይጠቀሳሉ። በኔዘርላንድስ በህክምና ታግዞ ራስን ማጥፋት ይቻላል። በአሜሪካ ያሉ ብዙ ግዛቶች እና የአውስትራሊያዋ ቪክቶሪያ በህክምና የታገዘ ሞትን ፈቅደዋል።
|
https://www.bbc.com/amharic/54744271
|
business
|
"የቻይናና የአሜሪካ ቀዝቃዛው ጦርነት ከኮሮናቫይረስ በላይ ለዓለም ያሰጋል"
|
በመጪዎቹ ዓመታት በአሜሪካና በቻይና መካከል ሊከሰት የሚችለው ቀዝቃዛ ጦርነት ዓለምን ከኮሮናቫይረስ በላይ ሊያስጨንቅ እንደሚገባ ዕውቁ የምጣኔ ሀብት ሊቅ ጄፍሪ ሳክስ ተናገሩ። የኮሎምቢያው ዩኒቨርስቲ ዕውቅ ፕሮፌሰር ጄፍ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ዓለም ወደ አንዳች መደነቃቀፍ እያመራች ነው፤ መሪ አልባም ሆናለች ብለዋል። እንዲሁም የዓለም ሁኔታ መልክ ባልያዘበት ሁኔታ በሁለቱ የዓለም ኃያላን መካከል ያለው ቁርሾና ቅራኔ እየባሰ ከሄደ ሁኔታዎችን ያባብሳል፤ ጦሱም ለተቀረው ዓለም ይተርፋል ብለዋል። እኚህ ፕሮፌሰር ለዚህ ሁሉ ተጠያቂዋ አሜሪካና አመራሯ ነው ብለዋል። • አገራዊ መድረክ ማዘጋጀት እንጂ ከህወሓት ጋር በድብቅ የሚደረግ ውይይትን አንቀበልም፡ ደብረፅዮን (ዶ/ር) • "አባላቶቻችን በአካባቢው ይህን የደንብ ልብስ መልበስ ካቆሙ ስድስት ወራት አልፈዋል" የኦሮሚያ ፖሊስ አሁን ያለው የአሜሪካ አመራር ከትብብር ይልቅ ክፍፍልን የሚያፋፍም ነው ሲሉም ለቢቢሲ ተናግረዋል። "አመራሩ አዲስ ቀዝቃዛ ጦርነት ከቻይና ጋር ለመፍጠር እየሞከረ ነው። ይህ ከሆነ ደግሞ ዓለምን ዳግም ወደ ሰላም ለመመለስ በጣም ይቸገራል" ብለዋል ፕሮፌሰሩ። የፕሮፌሰር ጄፍሪ ሳክስ አስተያየት የመጣው ሰሞኑን ቻይናና አሜሪካ ከምጣኔ ሀብት ጦርነት ጋር ብቻም ሳይሆን ፖለቲካዊ መቆራቆዝ ውስጥ እየገቡ ስለመሆኑ ምልክቶች መታየታቸውን ተከትሎ ነው። በያዝነው ሳምንት ለምሳሌ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካ በቻይና ባለሥልጣናት ላይ ማዕቀብ የሚጥለው ሰነድ ላይ ይፈርማሉ ተብሏል። ማዕቀቡን የሚጥሉት በዢንጂያንግ ግዛት የቻይና ሙስሊሞችን ለርዕዮተ ዓለም ጥምቀት ማጎርያ ውስጥ መከተታቸውን ተከትሎ ነው። ያም ሆኖ የዶናልድ ትራምፕ የቀድሞው የደኅንነት አማካሪ ሰሞኑን ለአንባቢዎች ያደርሱታል በተባለው አዲስ መጽሐፋቸው እንደጠቀሱት፤ ፕሬዝዳንቱ ቻይና ይህንን የሙስሊሞች ማጎርያ እንድትገነባ አበረታተው ነበር። ዶናልድ ትራምፕ ከሰሞኑ ከዎልስትሪት ጆርናል ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ቻይና ኮሮናቫይረስን ለዓለም ያቀበለችውና ብሎም ያሰራጨችው ሆን ብላ የአሜሪካንን ምጣኔ ሀብት ለማንኮታኮት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የቻይናና የአሜሪካንን የኢኮኖሚ ጦርነት ካመላከቱ ነገሮች አንዱ አሜሪካ በቻይናው ግዙፍ የቴሌኮም ኩባንያ ሁዋዌ ላይ የጣለችው እቀባ ነው። አሜሪካ እንደምትለው ሁዋዌ የደንበኞችን መረጃ ለመሰለል የተቋቋመ ነው። ቻይና ይህንን ክስ ታስተባብላለች። የቀድሞው የዶናልድ ትራምፕ ከፍተኛ የደኅንነት አማካሪ ጆን ቦልተን አዲስ በጻፉት መጽሐፍ እንዳጋለጡት ከሆነ ዶናልድ ትራምፕ ህዋዌ ላይ እቀባ ያደረጉት በድጋሚ የመመረጥ ዕድላቸውን ለማስፋት ብቻ ነው። • ትራምፕ እንዳይታተም ባሉት መጽሐፍ ይፋ የሚደረጉ 6 ምስጢሮች • በህዳሴው ግድብ ዙሪያ የሚደረገው ድርድር፡ የግብፅ ፍላጎትና የኢትዮጵያ ውሳኔ ፕሮፌሰር ጄፍሪ ሳክስም በዚህ የቦልተን ሐሳብ ይስማማሉ። ሁዋዌን ትራምፕ ያገዱት የምርም የደኅንነት ጉዳይ አሳስቧቸው ሊሆን አይችልም። "አሜሪካ በ5ጂ የሞባይል ቴክኖሎጂ ተቀድማለች። ሁዋዌ ደግሞ የዓለምን የገበያ ድርሻ ተቀራምቶታል፤ ይህ ነው አሜሪካንን የረበሻት" ይላሉ። ከቻይና ጋር ፍጥጫ ላይ ያለችው አገር አሜሪካ ብቻ አይደለችም። ቻይና ባለፈው ሳምንት ከሕንድ ጋር የድንበር ግጭት ውስጥ ገብታ 20 የሕንድ ወታደሮችን መገደላቸው አይዘነጋም። ይህ በእንዲህ እናዳለ ቻይና በፓኪስታን፣ በምያንማር፣ በሲሪሊንካና በኔፓል በርካታ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን እያገዘች ነው። እነዚህ አገራት ደግሞ የሕንድ ጎረቤቶች ናቸው። ሕንድ ቻይና የአካባቢው ተጽእኖ ፈጣሪ አገር የመሆኗን ጉዳይ ማስቆም ትፈልጋለች። ፕሮፌሰር ሳክስ እንደሚያምኑት ቻይና በአካባቢው አገራት ላይ የትብብር መንፈስ ካሳየች ነገሮች የተሻሉ ይሆናሉ። ቻይና እድሏ ያለው በእጇ ነው። ቻይና ተባባሪ ከሆነች፣ በዲፕሎማሲ ችግሮችን ለመፍታት ከፈለገችና የትብብር መንፈስ ካሳየች ጉልበት ያላት አገር ስለሆነች ብዙ ነገር መቀየር ትችላለች፤ የእሲያ አህጉርም የተሻለ መጻኢ እድል ይኖረዋል።
|
https://www.bbc.com/amharic/news-53135326
|
health
|
በኮሮና የተያዙ ሰዎች በድባቴ እና የመርሳት በሽታ የመጠቃት እድላቸው እንደሚጨምር ጥናት አመለከተ
|
ባለፈው ስድስት ወራት ውስጥ የኮሮናቫይረስ የያዛቸው ሰዎች በድባቴ፣ የመርሳት በሽታ፣ ስትሮክ እና በሳይኮሲስ ህመሞች የመጠቃት እድላቸው ከፍተኛ መሆኑን በኦክስፎርድ ተመራማሪዎች የተሰራ ጥናት አመላከተ። ከእነዚህ ውስጥ አንድ ሶስተኛው ቀድመው የነበሩባቸው የስነ ልቦና እና የነርቭ ችግሮች ያገረሽባቸዋል ወይም እንደ አዲስ ሕመሞቹ ያጠቋቸዋል ሲል ጥናቱ አመልክቷል። በቫይረሱ ተይዘው ሆስፒታል የገቡ ወይም በፅኑ ህሙማን ማቆያ ከነበሩ ደግሞ የመያዝ እድላቸው የበለጠ ይሰፋል ሲል ጥናቱ አመላክቷል። እነዚህ ጫናዎችም ጭንቀትን በማስከተል ወይም ቫይረሱ አዕምሮ ላይ በሚያስከትለው ቀጥተኛ ጫና ላይ ሊመሰረት እንደሚችልም አክሏል። እንግሊዛዊያን ሳይንቲስቶቹ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ በአሜሪካ የኮሮናቫይረስ ተጠቂዎችን የኤሌክትሮኒክ መረጃ በመመልከት እና በተለይም 14 ለሚሆኑ የስነ-ልቦና እና የነርቭ ችግሮች የመጋለጥ እድሎችን መርምረዋል። ከእነዚህም መካከል የአዕምሮ ውስጥ የደም መፍሰስ፣ ስትሮክ፣ ፓርኪንሰን፣ የመርሳት በሽታ፣ ሳይኮሲስ፣ የስሜት መቃወስ እና የጭንቀት ችግሮች ይገኙበታል፡፡ በጣም መታመምን ወይም ወደ ሆስፒታል መወሰድ ከሚያስከትለው የጭንቀት ጫና የተነሳ በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች ለጭንቀት እና የስሜት መቃወስ መዳረግ በተደጋጋሚ የታዩባቸው ችግሮች ናቸው ሲል ገልጿል። እንደ ስትሮክ እና የመርሳት በሽታ ያሉት ደግሞ ቫይረሱ በራሱ በሚያስከትለው አካላዊ ጉዳት ላይ ተመስርተው የሚከሰቱ ወይም ሰውነታችን ለቫይረሱ በሚሰጠው ምላሽ ምክንያት ሊከሰቱ ይችላሉ ሲልም አስረድቷል። ጥናቱ የኮሮናቫይረስ በቀጥታ ለፓርኪንሰን ወይም ለጊላይን-ባሬ ሲንድሮም የማጋለጥ እድሉን አላረጋገጠም። ምርምሩ ሁለት በጉንፋን የተያዙ ሰዎችን የያዙ ቡድኖችን በኮሮናቫይረስ ከተያዙት ጋር በማነፃፀር የተሰራ ሲሆን፣ ጥናቱን ያካሄዱት የኦክስፎርድ ዩኒቨርስቲ ተመራማሪዎች ኮሮና ከሌሎች የመተንፈሻ ህመሞች በበለጠ ከአዕምሮ ጉዳቶች ጋር እንደሚያያዝ ገልፀዋል። ቫይረሱ ወደ አዕምሮ ውስጥ እንደሚገባ እና ጉዳቶችን እንደሚያደርስ የሚያሳዩ ማስረጃዎች ተገኝተዋል ሲሉ ከተመራማሪዎቹ አንዱ የሆኑት የኦክስፎርዱ የኑሮሎጂ ፕሮፌሰር መሱድ ሃሰን አብራርተዋል፡፡ ከቀጥተኛ ጉዳቶችም ባሻገር የደም መርጋትን በማስከተሉ እና ይህም ስትሮክን ሊያመጣ እንደሚችል አክለዋል፡፡ በአጠቃላይም ሰውነታችን ቫይረሱን ለመከላከል ሲል የሚያደርገው ግብ ግብ አእምሮን ሊጎዳ ይችላል ሲሉም ገልፀዋል፡፡
|
https://www.bbc.com/amharic/news-56664358
|
sports
|
ለአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ከሁሉ ቀድመው ካሜሮን የገቡት ዋሊያዎች
|
በኮሮናቫይረስ ምክንያት በአንድ ዓመት የዘገየው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አሁንም በወረርሽኙ ስጋት ውስጥ ሆኖ በመጪው ወር ጥር 01/2014 ዓ.ም ካሜሩን ውስጥ መካሄድ ይጀምራል። በዚሁ ውድድር መሳተፋቸውን ያረጋገጡት ዋልያዎቹም ባለፈው ሳምንት እሁድ ከሁሉም የአፍሪካ አገራት ቀድመው ካሜሩን በመድረስ ዝግጅታቸውን ጀምረዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪው ጌታነህ ከበደን ጨምሮ 25 ተጫዋቾች በቡድኑ ውስጥ የተካተቱ ሲሆን፣ ካፍ ካስቀመጠው ገደብ በተጨማሪ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ሦስት ተጫዋቾች እንዲካተቱ ተደርጓ። ታኅሣሥ 14/ 2014 ይፋ ከተደረገው የብሔራዊ ቡድኑ 25 ተጫዋቾች ዝርዝር ከዚህ ቀደም በተጠባባቂነት ተይዘው የነበሩት ሱራፌል ዳኛቸው፣ ፍሬው ጌታሁን እና ይሁን እንደሻው ብሔራዊ ቡድኑን ተቀላቅለው ዋሊያዎቹ 28 ተጫዋቾችን በመያዝ ወደ ካሜሩን አቅንተዋል። የኢትዮጵያ የወንዶች ብሔራዊ ቡድን ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈው ከ8 ዓመታት በፊት ደቡብ አፍሪካ ባስተናገደችው ውድድር ላይ ነበር። ባለፈው እሁድ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፍያ የተነሳው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ልዑክ በቀዳሚነት የካሜሩን ሁለተኛ ከተማ ወደሆነችው ዱዋላ ደርሶ ለአንድ ሰዓት ከቆየ በኋላ ወደ ዋና ከተማዋ ያውንዴ ደርሷል። ብሔራዊ ቡድኑ ያውንዴ አየር ማረፊያ እንደደረሰ የኮቪድ-19 ምርመራን ያደረገ ሲሆን በመቀጠል ወደ ሆቴል ዴ ዴፕዩቴ አምርቶ ማረፊያውን ማድረጉን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን መረጃ ያሳያል። ብሔራዊ ቡድኑ እስካሁን ቀላል እና ጠንከር ያሉ አራት ልምምዶችን አከናውኗል። በዋሊያዎቹ ከሁሉ ቀድመው ለምን ወደ ካሜሩን ሄዱ? የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዋና ፀሐፊ አቶ ባህሩ ጥላሁን እንደሚሉት የመጀመሪያ እቅድ ተደርጎ የነበረው በመካከለኛው ምሥራቅ ከሚገኙ አገራት መካከል በአንዱ ውስጥ ዝግጅት ለማድረግ ነበር። "ከሳዑዲ አረቢያ እግር ኳስ ማኅበር ጋር ንግግሮች ነበሩ። እንዲያውም ሙሉ ወጪያችንን ሸፍነው እነሱ ጋር ሄደን እንድንዘጋጅ ተነጋግረን ነበር።" ነገር ግን የኮሮናቫይረስ ስርጭትን ተከትሎ የሳዑዲ አረቢያ መንግሥት የጉዞ እግዳዎችን ከጣለባቸው አገራት መካከል ኢትዮጵያ አንዷ በመሆኗ ሀሳቡ ሳይሳካ እንደቀረ ኃላፊው ለቢቢሲ ገልጸዋል። የሳዑዲ አረቢያ እግር ኳስ ፌደሬሽንም ቢሆን በተፈጠረው ነገር ማዘኑን እንደገለጸና ይቅርታ እንደመጠየቀም ኃላፊው አመልክተዋል። የመጀመሪያው እቅድ አለመሳካቱን ተከትሎ ደግሞ ፌደሬሽኑ ወደ ሁለተኛ እቅዱ ፊቱን ለማዞር ተገዷል። ይህም ደግሞ ወደ ምዕራብ አፍሪካ አገራት በመሄድ ልምምድ ማካሄድ ነበር። በስተመጨረሻም ወደ አዘጋጇ አገር ካሜሩን በመሄድ ልምምድ ለማድረግ ውሳኔ ላይ ተደርሷል። በተጨማሪም ብሔራዊ ቡድኑ ቀድሞ ወደ ካሜሩን ማቅናቱ የአገሪቱን የአየር ጸባይ ለመልመድ ይእንደሚረዳ የገለጹት አቶ ባሕሩ፣ የአፍሪካ ዋንጫ ዘንድሮ እንዳይካሄድ ከተለያዩ ወገኖች ግፊት ይደረግ ስለነበረ ያን በመቃወም ውድድሩ በተያዘለት ጊዜ እንዲከናወን ኢትዮጵያ ያላትን ድጋፍ ለማሳየት መሆኑን ጠቅሰዋል። ፊፋንና የአውሮፓ እግር ኳስ ማኅበርን ጨምሮ አንዳንድ የእግር ኳስ ማኅበራት የወረርሽኙን ስርጨት ተከትሎ የአፍሪካ ዋንጫ በዚህ ጊዜ መካሄድ የለበትም የሚል አስተያየት ሲሰጡ እንደነበር ዋና ፀሐፊው ተናግረዋል። "እኛ ደግሞ የፓንአፍሪካኒዝም ጀማሪዎች እንዲሁም የካፍ መስራች እንደመሆናችን ይሄ ውድድር በተያዘለት ጊዜ በካሜሩን እንደሚካሄድ ማረጋገጫ ለመስጠትና ይህንን መልዕክት ለማስተላለፍ ነው ቀድመን ወደ ካሜሩን ለማቅናት የወሰንነው።" ኦሚክሮን የተባለው አዲሱን የኮቪድ-19 ዝርያ በስፋት መሰራጨትን ተከትሎ በርካቶች ውድድሩ ላይካሄድ ይችላል በሚል ስጋታቸውን ቢገልጹም፣ የየካሜሩን መንግሥት እና የእግር ኳስ ማኅበሩ እንዲሁም የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ግን ጨዋታው በወጣለት መረሃ ግብር መሠረት እንደሚከናወን አረጋግጠዋል። ነገር ግን በካሜሩን በሚካሄደው የአፍሪካ እግር ኳስ ዋንጫ ላይ መታደም የሚችሉት የኮቪድ-19 ክትባትን ሙሉ ለሙሉ የወሰዱ እና ከቫይረሱ ነጻ መሆናቸው የተረጋገጠ ደጋፊዎች ብቻ እንደሚሆኑ አዘጋጆቹ ገልጸዋል። የካሜሩን ቆይታና ዝግጅት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሁን የሚገኘው የፊፋ ወኪል በሆነ ኤጀንት አማካይነት በተመቻቸ የስልጠና ካምፕ አገልግሎት መስጫ ውስጥ ነው። ይህ የስልጠና አገልግሎት መስጫ ካምፕ ሆቴል፣ መስተንግዶ፣ የስልጠና ቦታና ሌሎች አስፈላጊ ነገሮችን ሁሉ ያሟላ እንደሆነ አቶ ባህሩ ይገልጻሉ። "አሁን ብሔራዊ ቡድኑ ያለበት ቦታ ሁሉንም ፍላጎታቸውን የሚያሟላ ነው። አሁን ላይም ተጫዋቾቹ አስፈላጊውን ስልጠናና ዝግጅት በዚህ ማዕከል እያደረጉ ነው'' ሲሉ ዋሊያዎቹ ለውድድሩ አስፋለጊውን ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን አመልክተዋል። በአሁኑ ጊዜ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ዝግጅት ያውንዴ ከከተመ ሳምንት ሊሆነው ተቃርቧል። በቆይታውም መደበኛ ልምምድ በማድረግ ከሳምንት ለሚጀመረው ውድድር እየተዘጋጀ ነው። ከዚሁ ጋር ተያይዞም ከዋሊያዎቹ ቀጥሎ ካሜሩን ከደረሰው የሱዳን ብሔራዊ ቡድን ጋር ሐሙስ ዕለት የአቋም መፈተሻ ጨዋታ አድርጓል። በምድብ 'መ' ከግብፅ፣ ከናይጄሪያ እና ከጊኒ ቢሳዎ ጋር ከተደለደለችው ሱዳን ጋር በተደረገው የአቋም መለኪያ ጨዋታው አማኑኤል ገ/ሚካኤል ሁለት፣ ሽመልስ በቀለ ደግሞ አንድ ግቦችን አስቆጥረው ዋሊያዎቹ 3 ለ 2 በሆነ ውጤት ለማሸነፍ ችለዋል። ዋሊያዎቹ በካሜሩን በሚኖራቸው ቆይታ አጠቃላይ ወጪያቸውን የኢትዮጵያ መንግሥት ከፍተኛ ገንዘብ መድቦ እንደሚሸፍን የፌደሬሽኑ ዋና ፀሐፊ አቶ ባህሩ ጥላሁን ለቢቢሲ ገልጸዋል። የአፍሪካ አህጉር ትንቁ የእግር ኳስ ውድድር በሆነው ጨዋታ ላይ ኢትዮጵያን ወክሎ ለሚቀርበው ቡድን የሚያስፈልገውን ገንዘብ ፌዴሬሽኑ ከመንግሥት አግኝቷል። "ለዚህ ውድድር 51 ሚሊየን ብር እንዲመድብ ጠይቀን 35 ሚሊየን ብር ጸድቆልናል። በዚህ ገንዘብ ነው ብሔራዊ ቡድኑ እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው። በዚህ አጋጣሚ መንግሥት ላደረገው ነገር በሙሉ ፌዴሬሽኑ ያመስግናል'' ብለዋል አቶ ባሕሩ። ከዋሊያዎቹ ምን እንጠብቅ? የአፍሪካ እግር ኳስ ውድድር መስራች የሆነችው ኢትዮጵያ ከውድድሩ ርቃ ከመቆየቷ በተጨማሪ ከአንድ ጊዜ በላይ የጎላ ውጤትን ሳታስመዘገብ ቆይታለች። በዚህ 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የሚሳታፈው ቡድን ግን ይህንን ታሪክ የመቀየር ከፍ ያለ ፍላጎት አለው። ለዚህም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ከዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋሊያዎቹ በምድብ ጨዋታዎች ጥሩ ውጤት አስመዝግበው ከምድባቸው ማለፍን በቀዳሚነት የሚጠበቅ ውጤት እንደሆነ አቶ ባህሩ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ በምድብ አንድ ከአዘጋጇ ካሜሩን፣ ከቡርኪና ፋሶ እና ኬፕ ቬርድ ጋር ተደልድሏል። በዚህ ሂደትም ዋሊያዎቹ ከምድባቸው ወደቀጣይ ዙር ማለፍን የመጀመሪያ ግብ ከመሆኑ ጎን ለጎን "በስፖርት ዲፐሎማሲው ዘርም ሌሎች ኃላፊነቶችን እንመዲወስዱም" አቶ ባሕሩ ጠቅሰው "ኢትዮጵያን ለዓለም ሕዝብ በደንብ ማስተዋወቅና ማሳየት እንፈልጋለን። በዚህ ትልቅ አጋጣሚ አንድነታችንን ለመላው ዓለም በደንብ አድርገን እናሳያለን" ብለዋል። በተጨማሪም ካሜሩን ውስጥ 20 የሚደርሱ የኢትዮጵያውያን ስብስቦች እንደሚገኙ የገለጹት አቶ ባህሩ እነዚህን ኢትዮጵያውያን በማሰባብ ለብሔራዊ ቡድኑ ድጋፍ እንዲያደርጉ፣ እንዲሁም ከ500 በላይ የሚሆኑ ደጋፊዎች ከኢትዮጵያ ወደ ካሜሩን ለመጓዝ እየተዘጋጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። የዋሊያዎቹ ስብስብ ግብ ጠባቂዎች፡ ተክለማርያም ሻንቆ ከሲዳማ ቡና፣ ፋሲል ገብረሚካኤል ከባሕር ዳር ከተማ፣ ጀማል ጣሰው ከአዳማ ከተማ እንዲሁም ፍሬው ጌታሁን ከድሬዳዋ ከተማ ናቸው። ተከላካዮች፡ አስራት ቱንጆ ከኢትዮጵያ ቡና፣ ሱሌማን ሐሚድ ከቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ረመዳን የሱፍ ከወልቂጤ ከተማ፣ ደስታ ዮሐንስ ከአዳማ ከተማ፣ አስቻለው ታመነ ከፋሲል ከነማ፣ ያሬድ ባየህ ከፋሲል ከነማ፣ ምኞት ደበበ ከቅዱስ ጊዮርጊስ እና መናፍ አወል ከባሕር ዳር ከተማ። አማካዮች፡ አማኑኤል ዮሐንስ ከኢትዮጵያ ቡና፣ ጋቶች ፓኖም ከቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ሽመልስ በቀለ ከአል ጎውና፣ መስዑድ መሐመድ ከጅማ አባጅፋር፣ ሱራፌል ዳኛቸው ከፋሲል ከነማ፣ ፍጹም ዓለሙ ከባሕር ዳር ከተማ፣ ፍሬው ሰለሞን ከሲዳማ ቡና፣ በዛብህ መላዮ ከፋሲል ከነማ እንዲሁም ይሁን እንደሻው ከፋሲል ከነማ። አጥቂዎች፡ አቡበክር ናስር ከኢትዮጵያ ቡና፣ ጌታን ከበደ ከወልቂጤ ከተማ፣ አማኑኤል ገ/ሚካኤል ከቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ሽመክት ጉግሳ ከፋሲል ከነማ፣ ሙጂብ ቃሲም ከጄይኒስ ስፖርቲቭ ዲ ካቢሌ፣ መስፍን ታደሰ ከሐዋሳ ከተማ እንዲሁም ዳዋ ሁጤሳ ከአዳማ ከተማ ተመርጠዋል። ዋሊያዎቹ በካሜሩን ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ዋንጫ የደረሰችው ከዘጠኝ ዓመታት ቆይታ በኋላ ነው። በ1962 (እአአ) የአህጉሪቱን ትልቁን ዋንጫ ያነሱት ዋሊያዎቹ በአፍሪካ ዋንጫ ሲሳተፉ ይህኛው ለ11ኛ ጊዜ ነው። በዓለም እግር ኳስ 137ኛ ደረጃ ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ በአሠልጣኝ ውበቱ አባተና በአምበሉ ጌታነህ ከበደ እየተመራች ወደ ያውንዴ አቅንታለች። ይህ የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ለአሠልጣኝ ውበቱ አባቱና ለቡድኑ አባላት ከአፍሪካ ዋንጫ መሥራቾች አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ ያላትን ተሰጥዖ የሚያሳዩበት መድረክ እንደሚሆን ይገመታል። ውበቱ ለዓይን ገዥ የሆነውን ኳስ እግር ላይ ሳይቆዩ እየተቀባበሉ መጫወትን የሚመርጥ አሠልጣኝ ነው። የመሃል ሜዳው ሞተር ሽመልስ በቀለና አጥቂው ጌታነህ ከበደ ከወጣቱ የኢትዮጵያ ቡና አጥቂ አቡበከር ናስር ጋር በመጣመር ለተቀናቃኞቻቸው አደጋ ሊሆኑ ይችላሉ። ውበቱ በሚመርጠው የ4-3-3 አሠላለፍ ማለትም 4 የኋላ ደጀን ሦስት አማካዮችና ሦስት አጥቂዎች ተመርቶ ወደ ሜዳ እንደሚገባ ይገመታል። ብሔራዊ ቡድኗን በውበቱ አባተ እያጠናከረች ያለችው ኢትዮጵያ ወደ ዙር 16 መሻገር እንደ ትልቅ ውጤት ቢታይ የሚገርም አይሆንም። አልፎም ብሔራዊ ቡድናቸው በአፍሪካ ትልቁ ውድድር ሲሳተፍ ማየት ለጓጉ ኢትዮጵያዊያን ይህ ትልቅ ዕድል ነው።
|
https://www.bbc.com/amharic/news-59840259
|
health
|
የተከተቡ ሰዎች ለምን በድጋሚ ኮሮናቫይረስ ይይዛቸዋል?
|
ኮቪድ የሰው ልጅን የሙጥኝ እንዳለ አለ። አሜሪካ፣ ፈረንሳይ፣ ዩናይትድ ኪንግደም፣ አርጀንቲና፣ ብራዚል እና ሌሎም አገራት ውስጥ ኦሚክሮን ተመልሶ እያመሳቸው ነው። በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የሆስፒታል አልጋን እየያዙ ነው። ከእነዚህ የሚበዙት የተከተቡ ናቸው። ታዲያ መከተብ ከተህዋሲው ካልተከላከለ ምንድነው ፋይዳው? እርግጥ ነው ተከተቡ በተባሉ ሰዎች የሚታይ የጎንዮሽ ጉዳት ዝቅተኛ ነው። ብዙ ሰዎች በድኅረ ክትባት ጊዜ ከትኩሳት፣ ከራስ ምታት፣ ከክንድ መለስተኛ ሕመም፣ ከድካምና ከማቅለሽለሽ የከፋ ስሜት አይሰማቸውም። በክትባቱ ታይተዋል የሚባሉት አናፊላክሲስ፣ ቶምቦሲስ፣ ሚዮካርዲቲስ (የልብ አካባቢ መለብለብ) ወዘተ እጅግ ቁጥሩ ባነሱ ተከታቢ ሰዎች ዘንድ ብቻ ነው የተስተዋሉት። አሁን ድፍን ዓለም እየጠየቀ ያለው ጥያቄ ግን አንድ ነው። መከተብ ከተህዋሲው መያዝ ካላዳነ ምንድነው ፋይዳው? የሚል። ቢቢሲ ከሕጻናት ሕክምና አዋቂና የተላላፊ በሽታዎች አጥኚ ሬናቶ ክፎሪ ጋር በዚህ ጉዳይ ላይ ቆይታ አድርጎ ነበር። እሳቸው እንደሚሉት ከሆነ በመጀመሪያው ምዕራፍ ላይ እነ ፋይዘር እና አስትራዜኒካ እንዲሁም ጆንሰን ኤንድ ጆንሰን ክትባታቸውን ሲያበለጽጉ ግብ የነበረው ተህዋሲው ሰዎችን ለከፋ የጤና ችግር እንዳይዳርጋቸው፣ ሲከፋ ደግሞ ለሞት እንዳያበቃቸው እንጂ ተህዋሲው እንዳይዛቸው ለማድረግ አልነበረም። ሐኪሙ ይህ ግባቸው ተሳክቷል ብለው ያምናሉ። "ክትባቶቹ እጅግ ለከፋው የጤና ችግር አጋላጭ ሁኔታ በቂና አስተማማኝ ምላሽ ይሰጣሉ። ቀላልና መለስተኛ ለሆኑ የተህዋሲው ምልክቶች ደግሞ ክትባቶቹ እምብዛምም ናቸው።" እንደ ሐኪሙ ማብራሪያ መጀመሪያውኑም እኮ ክትባቶቹ ሥሪታቸው ወረርሽኙን ማቆም ወይም ሰው በተህዋሲው መልሶ እንዳይያዝ ማድረግ አልነበረም ይላሉ። "ዋናው የክትባቶቹ ተልዕኮ አንድ ነው። ተህዋሲው ሰውነትን ለከፋ አደጋ ብሎም ለሞት እንዳያበቃ ጉዳቱን መቀነስ ነበር፤ ይህም ስኬታማ ነው" ይላሉ። እንደ ምሳሌ የሚያቀርቡት በተለምዶ የጉንፋን ማስታገሻ የምንለው ክትባትን ነው። ያ ክትባት ለዘመናት ሲሰጥ ነው የተኖረው። አንድም ጊዜ ግን ጉንፋኑን ለማጥፋት ተብሎ አግልግሎት ላይ አልዋለም። ሰዎች በጉንፋን የተነሳ ወደከፋ ደዌ እንዳይወደቁ ማገዝ ነው ተግባሩ። ይህ ክትባት ኢንፍሌዌንዛን ለማጥፋት አልተመረተም። ነገር ግን ልጆች፣ ነፍሰጡሮች፣ ሽማግሌዎች እና ገመምተኞች ይህ የኢንፍሌውዛ ተህዋሲዊ ችግር ውስጥ እንዳይጥላቸው ያደርጋቸዋል። የኮቪድ-19 ክትባትም ተመሳሳይ ነው። ወረርሽኝ የማቆም ተልዕኮ የለውም ይላሉ። የኮቪድ-19 ክትባቶች ምን ያህል ሞትን ታድገዋል የሚለውን ብንመለከት ይህን የሐኪሙን ሙግት የሚደግፍ ሆኖ እናገኘዋለን። የኮመንዌልዝ ፈንድ ባወጣው አንድ ሰነድ ላይ እንደተመላከተው ኮሮናቫይረስ ክትባቶች ባለፈው የአውሮፓውያን ዓመት ብቻ አንድ ሚሊዮን ሞትን ተከላክሏል። ነገር ግን 10 ሚሊዮን ሰዎች ደግሞ ሆስፒታል እንዳይገቡና አልጋ እንዳይዙ የሆኑት ክትባት በመውሰዳቸው ነው። ይህ አሐዝ የአሜሪካንን ሕዝብ ብቻ ግምት ውስጥ ያስገባ ነው። የዓለም ጤና ድርጅትና የአውሮፓ የተላላፊ በሽታ ቁጥጥጥር ማዕከል እንደሚገምቱት ደግሞ ግማሽ ሚሊዮን የሚሆኑ ዕድሜያቸው ከ60 ዓመት በላይ የሆኑ፣ በ33 የአውሮፓ አገራት የሚኖሩ ዜጎች ክትባቱ ከሞት ታድጓቸዋል። ይህ በሌላ አነጋገር ሲገለጽ እነዚህ ሰዎች ክትባቱን በወቅቱ ባይከተቡ ኖሮ የመሞት ዕድላቸው ሰፊ ነበር። ከእነዚህ መካከል ምናልባትም በርካታ ሰዎች ተህዋሲው መልሶ አልያዛቸውም ባይባልም፣ ለከፋ ጉዳት እንዳያደርሳቸው የሆነው ግን በመከተባቸውና በመከተባቸው ብቻ ነው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተከተቡ ሰዎች ለምን በተህዋሲው በብዛት መያዝ ጀመሩ? ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሙሉ ክትባት የወሰዱ ሰዎች ሳይቀር በኦሚክሮን እየተያዙ እንደሆነ የሚስተባበል ጉዳይ አይደለም። ይህ በሦስት ምክንያት ሊሆን እንደሚችል ይገመታል። በተለይ በምዕራቡ ዓለም ገና እና አዲስ ዓመት ክብረ በዓል ላይ በርካታ ሰዎች በጋራ ብዙ ተቀራርበዋል። ይህ መቀራረብ ተህዋሲው እንደልብ እንዲዛመት ሳያስችለው አልቀረም። ሁለተኛው ምክንያት ክትባቱ ለተቀረው ዓለም ከተሰራጨ ከዓመት በኋላ ተመራማሪዎች የደረሱበት አንድ ፍንትው ያለ ሐቅ ቢኖር፣ ክትባቱ አንድ ጊዜ ተወስዶ በቃ ከዚህ ወዲያ እምብዛም አያስፈልግም የሚባል እንዳልሆነ ነው። "በጊዜ ሂደት የክትባቱ የመከላከል አቅም እንደሚወርድ ደርሰንበታል። አቅሙ የመውረዱ ፍጥነት ደግሞ ከተከታቢው ዕድሜና የተፈጥሮ ሁኔታ ጋር የተያያዘ ነው" ይላሉ ሐኪም ክፎሪ። ይህም ሐቅ ነው ሦስተኛ ዙር የማጠናከሪያ ክትባት ዘመቻ እንዲከፈት ምክንያት የሆነው። ይህ ዘመቻ በቅድሚያ ዕድሜያቸው ለገፋ ብቻ ታስቦ የነበረ ቢሆንም ሌሎች ሰዎችም ቢወስዱት ጥቅም እንጂ ጉዳት እንደሌለው ተደርሶበታል። ያም ሆኖ አሁንም የተከተቡ ሰዎች በተህዋሲው እየተያዙ ነው ያሉት። በዚህ ጉዳይ ላይ ሐኪሙ የሚሉት ይህንን ነው። "ነገሩ እንደ ኢንፍሌዎንዛ ክትባት ነው። ከዚህ ሁኔታ ጋር፣ ከሐቁ ጋር ተስማምተን መኖር መቀጠል ነው የሚኖርብን። ሌላ ነገር የለም።" መልካሙ ነገር ተከትበው ሳለ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በመጣው ልውጥ የኮሮናቫይረስ ምክንያት ወደ ሆስፒታል የሚመጡ ሰዎች ቁጥር እዚህ ግባ የሚባል አለመሆኑ ነው። ይህም የሚያሳየው ክትባቱ ይነስም ይብዛ ሥራውን እየሠራ መሆኑን ነው። ይህን ሐቅ ለማስረዳት ኒውዮርክ ከተማን እንደ ማሳያ መውሰድ ብቻ በቂ ነው። በታኅሣሥ ወር ወደ ሆስፒታል የሚመጡ ሰዎች እና የሟቾች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ አሻቀበ። ከእነዚህ ውስጥ እጅግ የበዙት ክትባት ያልወሰዱ ናቸው። ክትባት የወሰዱ ሰዎች ግን በተህዋሲው ቢያዙም ለሆስፒታል የሚያበቃ ችግር ላይ አልወደቁም። የዩናይትድ ኪንግደም ጤና ቢሮም ቢሆን ከዚህ የተለየ ድምዳሜ ላይ አልደረሰም። የኬምብሪጅ ዩኒቨርስቲ ባወጣው አንድ የጥናት አሐዝ አንድ ሙሉ ጠብታ የተከተበ ሰው በኦሚክሮን ቢያዝ ወደ ሆስፒታል የማይመጣበት ዕድል 81 ከመቶ በላይ ነው። ሐኪሙ የመጨረሻ መልዕክታቸው ይህ ነው። "ብከተብም ባልከተብም ያው በቫይረሱ መያዜ አይቀርምና ቢቀርብኝስ የሚሉት ሰዎች ፍጹም የተሳሳቱ ናቸው። እውነት ነው፣ የተከተበም ያልተከተበም በተህዋሲው ሊያዝ ይችላል። ነገር ግን ውጤታቸው አንድ አይደለም። የተከተቡት በቤታቸው ያልፉታል፤ ያልተከተቡት ግን ይሞታሉ።"
|
https://www.bbc.com/amharic/news-59925005
|
politics
|
ኡጋንዳ ከሙዚቀኛው ተቃዋሚ ጋር ግንኙነት ያላቸው የዩቲዩብ ቻናሎች እንዲታገዱ ጠየቀች
|
የኡጋንዳ መንግሥት ከታዋቂው ሙዚቀኛና ተቃዋሚ ቦቢ ዋይን ግንኙነት ያላቸው የዩቲዩብ ቻናሎች እንዲታገዱ ጠይቋል። በኡጋንዳ የኮሚዩኒኬሽን ዘርፉን በዋነኝነት የሚቆጣጠረው አካል አስራ አራት የዩቲየብ ቻናሎች እንዲዘጉ ጠይቋል። ተቆጣጣሪው አካል ደብዳቤውን የፃፈው የዩቲዩብ ባለቤት ለሆነው ጉግል ሲሆን በባለፈው ወር ከደረስው ነውጥም ጋር ግንኙነት ያላቸውና ለ50 ሰዎችም መሞት ተጠያቂ ናቸው ያላቸው እንደሆነም አስፍሯል። በአገሪቱ ውስጥ ዋነኛ ተቃዋሚ የሚባለው ሮበርት ካያጉላንይ ወይም ቦቢ ዋይን እስር ተከትሎም በመዲናዋም ካምፓላም ሆነ በዋነኞቹ ከተሞች ነውጥ ተከስቷል። ሙዚቀኛው ቦቢ ዋይን የኮሮናቫይረስ መመሪያዎችን ጥሷል በሚልም ነው ለእስር የተዳረገው። እንዲታገዱ የተወሰኑት የዩቲዩብ ቻናሎች ከሙዚቀኛው ጋር ግንኙነት አላቸው ቢባልም የኡጋንዳ ኮሚዩኒኬሽን የህግ ጉዳዮች ኃላፊ በበኩላቸው "የአጋጣሚ ጉዳይ ነው" ማለታቸውን ብሉምበርግ ዘግቧል። ኮሚሽኑ ለጉግል በፃፈው ደብዳቤ የዩቲብ ቻናሎቹን ነውጡን ለማነሳሳት ተጠቅመውበታል፤ ከህግ ውጭ ያላቸውንም ይዘቶች አሳይተዋል በማለትም ዴይሊ ሞኒተር ጋዜጣ ፅፏል። ኡጋንዳ በጥር ወር ምርጫዋን ለማካሄድ በዝግጅት ላይ ናት። አገሪቷን ከሶስት አስርት አመታት በላይ የመሯት ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪንም በምርጫው ይወዳደራሉ።
|
https://www.bbc.com/amharic/news-55329580
|
sports
|
እግር ኳስ፡ አምስት ቁልፍ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች በኮሮናቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ
|
ኢትዮጵያ ጥቅምት ወር መጨረሻ ላይ ለአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ውድድር ከኒጀር ጋር ለምታደርገው የደርሶ መልስ ጨዋታ ተጠርተው ከነበሩት ተጫዋቾች መካከል አምስት ቁልፍ ተጫዋቾች ኮቪድ-19 እንደተገኘባቸው ተነገረ። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ባህሩ ጥላሁን ለቢቢሲ እንዳረጋገጡት ለብሔራዊ ቡድኑ ተጠርተው ከነበሩት 36 ተጫዋቾች መካከል ለቡድኑ ወሳኝ የሆኑት አምስት ተጫዋቾች በተደረገላቸው ምርመራ የኮሮናቫይረስ ተገኝቶባቸዋል። አቶ ባህሩ ለውድድሩ 41 ተጫዋቾች መጠራታቸውን አስታውሰው፣ አምስቱ በተለያየ ምክንያት ቡድኑን አለመቀላቀላቸውን አመልክተዋል። ከአምስቱ መካከል ሁለቱ በአሁን ሰዓት በውጭ አገር በሙከራና በመጫወት ላይ የሚገኙ ተጫዋቾች ናቸው ብለዋል። ኃላፊው አክለውም ሁለት ተጫዋቾች ዘግይተው ቡድኑን መቀላቀላቸውን ገልፀው፤ አንደኛው ደግሞ ከዚህ ቀደም በነበረበት ጉዳት ምክንያት ቡድኑን መቀላለቀል ያልቸለ መሆኑን ተናግረዋል። ለእግር ኳስ ቡድኑ አባላት የኮቪድ-19 ምርመራ ከመደረጉ በፊት የልብ ምርመራን ጨምሮ አጠቃላይ የጤና ምርመራ መደረጉን የተናገሩት ኃላፊው፤ የኮቪድ-19 ምርመራውም ለሁሉም መሰጠቱን ገልጸዋል። በዚህም መሠረት ለብሔራዊ ቡድኑ ለተጠሩት ለአጠቃላዩ 36 ተጫዋቾች የኮሮናቫይረስ ምርመራ ተደርጎ አምስት ተጫዋቾች ላይ ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል ብለዋል አቶ ባሕሩ። ቫይረሱ ከተገኘባቸው ተጫዋቾች ጋር ንክኪ አላቸው የተባሉትን የመለየት ሥራ እየተሰራም መሆኑን ጨምረው አመልክተዋል። እነዚህ ቫይረሱ የተገኘባቸው አምስት ተጫዋቾች በአሁኑ ጊዜ በሆቴል ራሳቸውን ለይተው እንዲቆዩ መደረጉን በመግለጽ፣ ልምምድ እየሰሩ በቶሎ እንዲያገግሙ ፌዴሬሽኑ የተቻለውን ሁሉ እያደረገ መሆን አብራርተዋል። የአምስቱ ተጫዋቾች ውጤት እንደተሰማ በቡድኑ አባላት መካከል ድንጋጤ ተፈጥሮ የነበረ ቢሆንም ከኅብረተሰብ ጤና ኢንስትትዩት የመጡ ባለሙያዎች ሙያዊ ምክር እንደሰጧቸውም ተገልጿል። እነዚህ በኮቪድ-19 የተያዙ አምስት ተጫዋቾች ለለይቶ ማቆያነት ፈቃድ ወደ ተሰጣቸው ሆቴሎች ዛሬ፣ ሰኞ፣ እንደሚዛወሩም ኃፊው አክለው ተናግረዋል። አምስቱ ተጫዋቾች በቡድኑ ውስጥ ቁልፍ ሚና እንደነበራቸው ያስታወሱት አቶ ባሕሩ በቡድኑ ላይ የሥነ ልቦና ጫና ቢኖረውም ቶሎ አገግመው ወደ ቡድኑ እንዲቀላቀሉ ይደረጋል ብለዋል። ተጫዋቾቹ ከ14 ቀን ለይቶ ማቆያ በኋላ ለጨዋታው ይደርሳሉ ተብሎ እንደሚገመት ተናግረው፣ እነዚህን ተጫዋቾች ወደ ቡድኑ የመቀላቀል ውሳኔ ግን የአሰልጣኙ መሆኑን አስረድተዋል። ቀሪ የቡድኑ አባላትን ከኮሮናቫይረስ ለመጠበቅ የተለያዩ የጥንቃቄ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑንም አብራርተዋል። ኢትዮጵያ ከኒጀር ጋር የሚኖራት ጨዋታ የሚካሄደው ጥቅምት 30/2013 ዓ.ም መሆኑ ኃላፊው ጨምረው ገልፀዋል። በተያያዘ ዜና ከኮሮናቫይረስ ስጋት ጋር በተያያዘ ተቆርጠው የቆዩት ከፍተኛ ሊግ፣ አንደኛ ሊግና የሴቶች ፕሪሚየር ሊግን ኅዳር አጋማሽ ላይ ለመጀመር የእግር ስ ፌዴሬሽኑ አቅዶ ለቡድኖች ማሳወቁንና እነርሱም ዝግጅት ማድረጋቸውን አክለው ተናግረዋል። ውድድሮቹ የሚካሄዱት በዝግ ስታዲየም መሆኑን ገልፀው በሂደት አማራጮች እየታዩ ደጋፊዎች የሚገቡበት ሁኔታ ይፈቀዳል ብለው እንደሚያስቡ ለቢቢሲ አቶ ባሕሩ ጥላሁን ተናግረዋል።
|
https://www.bbc.com/amharic/news-54417243
|
health
|
ኮሮናቫይረስ፡ በኦክስጂን እጥረት በርካቶች በሚሞቱባት ሕንድ ሆስፒታል ላይ በተነሳ እሳት 13 ህሙማን ሞቱ
|
ዛሬ አርብ በሕንዷ ከተማ ሙምባይ አቅራቢያ ባለ ኮቪድ-19 ህክምና ሆስፒታል ላይ በተነሳ ቢያንስ 13 ሰዎች መሞታቸው ተነገረ። አርብ ጠዋት የተቀሰቀሰው እሳት ለበርካቶች ሞት ምክንያት ከሆነ በኋላ በቁጥጥር ሰር የዋለ ሲሆን ከአደጋው ተረፉት ህሙማን በአቅራቢያ ወደሚገኝ ሆስፒታል ተዘዋውረዋል። በርካታ ሰዎች በወረርሽኙ እየተያዙባት ባለችው ሕንድ በዛሬው ዕለት ብቻ 332,730 ሰዎች ላይ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሲሆን ይህም በዓለም በአንድ ቀን የተመዘገበው የህሙማን ቁጥር ነው ተብሏል። በበሽታው ሰበብ ህይወታቸው ሚያልፍ ሰዎች አሃዝም እጅግ ከፍተኛ ሲሆን ባለፉት 24 ሰዓታት 2,263 ሰዎች መሞታቸው ተገልጿል። በሕንድ ለሁለተኛ ጊዜ የተከሰተውን የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ተከትሎ በዋና ከተማዋ ኒው ደልሂ ያሉ ሆስፒታሎች ከፍተኛ የኦክስጂን እጥረት አጋጥሟቸዋል። በዚህም ኦክስጂን በመጠባበቅ ላይ የነበሩ ታማሚዎች ህይወት እያለፈ መሆኑን እና በሕንድ ምርጥ የተባለ የጤና መሰረተ ልማት ባያላት ኒው ደልሂ ከተማ ለጽኑ ህሙማን የሚሆኑ አልጋዎች ሞልተዋል ተብሏል። እስከ አሁን ድረስ 16 ሚሊዮን ዜጎቿ በኮሮናቫይረስ መያዛቸውን ሕንድ አረጋግጣለች። ትናንት ሐሙስ ይፋ የተደረገው የ24 ሰዓታት የምርመራ ውጤት ብቻ ከ314 ሺህ በላይ ሰዎች በአንድ ቀን በወረርሽኙ መያዛቸውን እና ከሁለት ሺህ በላይ ሰዎች መሞታቸውን ያሳያል። የሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስቴር ናሬንድራ ሞዲም በቫይረሱ ከባድ ጉዳት ከደረሰባቸው ግዛቶች መሪዎች እና ከኦክስጂን አምራቾች ጋር ዛሬ ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል። ከኒው ደልሂ ውጪ ጉጃራት፣ ኡታር ፕራዴሽ እና ሃርያና የተሰኙት ግዛቶች ተመሳሳይ የኦክስጂን እጥረት ገጥሟቸዋል። ግዛቶች የኦክስጂን መያዣ ጋኖች ወደ ሌሎች ግዛቶች እንዳይዘዋወሩ በማገድ ላይ ሲሆኑ፤ የተወሰኑ ተቋማት ምርቶቻቸውን ማከማቸት መጀመራቸውን የደልሂ ቴሌቪዥን ዘግቧል። በኮቪድ-19 ተይዞ በህክምና ላይ ያለው የሕንድ ፖለቲከኛ ሳውራህ ባራድዋጅ በትዊተር ገጹ የተገጠመለት ኦክስጂን ሊያልቅ የቀረው ሦስት ሰዓታት ብቻ መሆኑን አጋርቶ ነበር። "ብዙ ሰዎች በኦክስጅን ላይ ጥገኛ ሆነው ነው ያሉት። የተገጠመላቸው ኦክስጂን ሲጠናቀቅ ህይወታቸው ያልፋል። ይህ ጊዜ በጋራ ተባብረን የምንሰራበት ነው" ሲል ተማፅኗል። በበሽታው ምክንያት የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር ከፍተኛ በመሆኑ በሕንድ ባህል መሰረት የሞቱ ሰዎች አስከሬንን ለማቃጠል ከፍተኛ ወረፋ መኖሩን ቤተሰቦች ገልጸዋል። አንድ ሐኪም በሆስፒታ ውስጥ ተራ የሚጠብቁ በርካታ አስከሬኖች መኖራቸውንም ገልጿል።
|
https://www.bbc.com/amharic/news-56827449
|
sports
|
የጀርመን ቡንደስሊጋ ቡድኖች ለ'ብላክ ላይቭስ ማተር' ያላቸውን ድጋፍ አሳዩ
|
የጀርመን ቡንደስሊጋ የእግር ኳስ ቡድኖች ለ'ብላክ ላይቭስ ማተር' እንቅስቃሴ ያላቸውን ድጋፍ በትናንትናው ዕለት በተለያዩ ተቃውሞዎች አሳይተዋል። የብሮሲያ ዶርትሙንድና ሄርታ በርሊን ተጫዋቾች በሲግናል ኢዱና ፓርክ በመገኘት ሜዳውን በመክበብም በጉልበታቸው ተንበርክከው ነበር። የዶርትሙንድ ተጫዋቾች ከውድድሩ በፊት ሲያሟሙቁ "ፍትህ ከሌለ ሰላም የለም" እንዲሁም "ተባብረን እንቁም" የሚሉ መልእክቶች በተፃፈባቸው ማሊያዎች (ካናቴራዎች) ነው። የባየር ሙኒክ ተወዳዳሪዎች "ለዘረኝነት ቀይ ካርድ" የሚል ማሊያ (ካናቴራ) ለብሰው የነበረ ሲሆን፤ በዛኑ ዕለት ባየር ሌቨርኩሰንን 4 ለ2 በሆነ ውጤት ረትተዋል። የቡንደስሊጋ ቡድኑ አመራሮችም እንዲሁም የቡድኑ አባላት በጨዋታዎች ላይ 'ብላክ ላይቭስ ማተር' የሚል ፅሁፍ ያለበት እጃቸው ላይ አጥልቀው ነበር ተብሏል። የሜይንዝ ቡድን አጥቂ ካሜሮናዊው ፒየር ኩንዴ ከኤይንትራችት ፍራንክፈርት ጋር ባደረጉት ጨዋታም ላይ ጎል ካስቆጠረ በኋላ በጉልበቱ ተንበርክኳል። በግጥሚያው ቡድኑ 2 ለ0 ረትቷል። በዚህ ሳምንትም ታዋቂዎቹ የስፖርት ሰዎች ሴረና ዊልያምስ፣ ፓውል ፖግባና ሊውስ ሃሚልተን በአሜሪካ በጥቁሮች ላይ የሚፈፀመውን የፖሊስ ጭካኔ አስመልክቶ ድምፃቸውን አሰምተዋል። ባለፈው ሳምንት በሚኒያፖሊስ ጥቁር አሜሪካዊው ጆርጅ ፍሎይድ እጁ ከኋላ እንደተጠፈረ ከመሬት ላይ ተጣብቆ ነጭ ፖሊስ አንገቱን በጉልበቱ ለዘጠኝ ደቂቃ ተጭኖት ህይወቱ ማለፉን ተከትሎ በበርካታ ግዛቶች ተቃውሞች ተቀጣጥለዋል።
|
https://www.bbc.com/amharic/news-52954511
|
health
|
የአውሮፓ ዕለታዊ የኮቪድ ሞት ካለፈው ሳምንት አንጻር 40 በመቶ ከፍ ብሏል
|
በአውሮፓ በየቀኑ የሚመዘገበው የሞት መጠን ካለፈው ሳምንት ጋር ሲነፃፀር በ40 በመቶ መጨመሩን የዓለም ጤና ድርጅት ለቢቢሲ ገለጸ። የድርጅቱ ቃል አቀባይ ዶ/ር ማርጋሬት ሃሪስ እንደተናገሩት ፈረንሳይ፣ ስፔን፣ እንግሊዝ፣ ኔዘርላንድስ እና ሩሲያ በአንድ ሦስተኛ ባደገው ቁጥር ውስጥ ከፍተኛውን ድርሻ ይዘዋል። "በሆስፒታሎች ውስጥ የጽኑ ህሙማን የህክምና ክፍሎች በጣም በታመሙ ሰዎች መሞላት ጀምረዋል" ሲሉ አስጠንቅቀዋል። ሩሲያ በቀን 320 የሆነ ከፍተኛ ሞት በማስመዝገብ በአጠቃላይ በቫይረሱ ህይወታቸው ያጡ ሰዎች ቁጥር ከ26ሺህ በላይ አድርሶታል። ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በ 221 ሰዎች ሞት ምክንያት በጣሊያን ውስጥም እንዲሁ ከፍተኛ ጭማሪ ታይቷል። በአጠቃላይ በኦስትሪያ የሟቾች ቁጥር ማክሰኞ ከ 1000 በላይ ሆኗል። ጣሊያን ውስጥም ቁጥሩ በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሮ በሃያ አራት ሰዓታት ውስጥ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ወደ 22,000 ደርሰዋል። አዲስ የተጣለውን ገደብ በመቃወም ሰኞ አመሻሽ ላይ የተቃውሞ ሰልፎች በጣሊያን ተካሂደዋል። የዓለም ጤና ድርጅት ምን አለ? ከቢቢሲ ወርልድ ጋር ቆይታ ያደረጉት ያደረጉት ዶ/ር ሃሪስ "በመላው አውሮፓ የከፋ እና አስደንጋጭ በሆነ መልኩ በቫይረሱ የሚያዙ እና የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር ጭማሪ እያየን ነው" ብለዋል። ከቀደመው ሳምንት ጋር ሲነፃፀር በየቀኑ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር በአንድ ሦስተኛ ሲጨምር የሚመዘገበው የሞት መጠን በ40 በመቶ ከፍ ብሏል። "የሆስፒታሎችን አቅም በተሻለ መንገድ ማስተዳደር ቢቻልም በበርካታ አገራት የሚገኙ ሆስፒታሎች አልጋዎች በፍጥነት እየተያዙ ነው" ሲሉ አስጠንቅቀዋል። "በተወሰኑ የአውሮፓ አገራት ውስጥ የተጣሉ አዳዲስ ገደቦች ውጤታማነት የሚታወቀው በሁለት ሳምንት ጊዜ ውስጥ ነው" ብለዋል። ሩሲያ ከዛሬ ጀምሮ ሰዎች በሚበዙባቸው እንደ ትራንስፖርት አገልግሎት፣ ታክሲ እና አሳንሰር ያሉ ቦታዎች ላይ የአፍና አፍኝጫ መሸፈኛዎችን ማድረግን አስገዳጅ አድርጋለች። የፈረንሳይ መንግሥት በፓሪስ እና በሌሎች ከተሞች ውስጥ ቀድሞ የተጣሉትን እገዳዎች ማራዘምን ጨምሮ ጥብቅ እርምጃዎችን በመተግበር ላይ እየተወያየ ነው። ጣሊያን ካለፈው አርብ ጀምሮ ምግብና እና መጠጥ ቤቶች፣ የስፖርት መዝወተሪያ ስፍራዎች ና ሲኒማዎች ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ መዘጋታቸውን በመቃወም በቱሪን ሰልፍ ያደረጉ ዜጎች ከፖሊስ ጋር ተጋጭተው ፖሊስ በሰልፈኞች ላይ አስለቃሽ ጭስ ለመተኮስ ተገዷል።
|
https://www.bbc.com/amharic/54708506
|
health
|
የወባ በሽታ መከላከያ ክትባት ላይ የተደረገ ሙከራ ከፍተኛ ውጤት አሳየ
|
በኦክስፎርድ የኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች እና በቡርኪናፋሶ ሳይንቲስቶች በጋራ የተሰራ አዲስ የወባ በሽታ መከላከያ ክትባት በተደረገለት ሙከራ ውጤታማ መሆነ ተገለጸ። በክትባቱ ላይ በተደረጉት መጀመሪያ ሙከራዎች 77 በመቶ በሆነ ውጤት ስኬታማ መሆኑ የተነገረ ሲሆን፤ ይህም አሁን ለህክምና ከሚውሉ መድኃኒቶች አንጻር ውጤታማነቱ በእጅጉ የላቀ ነው ተብሏል። የህክምና ጉዳዮች መጽሔት በሆነው 'ላንሴት' ላይ የታተመው የጥናቱ ውጤት 450 ከቡርኪናፋሶ የተወጣጡ ህጻናት የተሳተፉበት ሲሆን ከዚህ በኋላ በርከት ያሉ ሰዎች የሚሳተፉበት ሙከራ ይደረግበታል። በቀጣዩ የሙከራ ሂደትም 4,800 ህጻናት የሚሳተፉ ሲሆን እነዚህም ከቡርኪናፋሶ፣ ከማሊ እና ከኬንያ ናቸው። "ይህ ሙከራ በጣም አስደሳች የሆነ ውጤታማነት ነው ያሳየው። ክትባቱ ከዚህ በፊት ከነበሩ ህክምናዊች አንጻር የተሻለ የመከላከል ብቃት አሳይቷል። "በመቀጠል የምናካሂዳቸውን ሁለተኛና ሦስተኛ ዙር ሙከራዎች እየተጠባበቅን ነው። በእነዚህ ሙከራዎች በርከት ያሉ ሰዎች የሚሳተፉ ሲሆን በስፋት ቢመረት ምን አይነት ውጤት እንደሚኖረው ለማወቅ ይረዳናል" ብለዋል በቡርኪናፋሶ የጤና ሳይንስ ተቋም ዳይሬክተር የሆኑት ሃሊዶ ቲንቶ። ለወባ በሽታ የሚሆን ክትባት ማግኘት በህክምና ምርምር ውስጥ እግጅ ትልቅ ዜና ነው የሚሆነው። ሙከራው በስኬት የሚጠናቀቅ ከሆነ ትልቅ ግኝት እንደሚሆን ይጠበቃል። የወባ በሽታ በዓመት ከ400 ሺህ በላይ ሰዎችን የሚገድል ሲሆን አብዛኛዎቹ ከሰሀራ በታች በሚገኙ የአፍሪካ አገራት ውስጥ የሚኖሩ ህጻናት ናቸው። በአሁኑ ጊዜ ለወባ በሽታ የሚሆን አንድ ክትባት ያለ ሲሆን ውጤታማነቱ ደግሞ 50 በመቶ ብቻ ነው። በአዲሱ ክትባት የመጀመሪያ ዙር ሙከራ ላይ 77 በመቶ ውጤታማነት የታየ ሲሆን በሌሎች አገራትም ላይ ለመሞከር ታቅዷል። በጊዜ ብዛት ደግሞ ቢያንስ በአራት የአፍሪካ አገራት ውስጥ ይሞከራል። በሙከራው የሚሳተፉት 5 ሺህ የሚሆኑ ህጻናት ደግሞ እድሜያቸው ከሦስት ዓመት በታች የሆኑ ናቸው። አሁን በሙከራ ላይ የሚገኘው አዲሱ ክትባት ሙሉ ፈቃድ አላገኘም። ነገር ግን ውጤታማነቱ በሙከራዎች በተገቢ ሁኔታ የሚረጋገጥ ከሆነ የበርካቶችን ህይወት የማትረፍ ትልቅ አቅም አለው ተብሏል።
|
https://www.bbc.com/amharic/news-56827450
|
business
|
መንግሥት በኦሮሚያ ባለው ታጣቂ ቡድን ላይ ጠንካራ ወታደራዊ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን ገለጸ
|
የመንግሥት ኃይል በተለያዩ የኦሮሚያ ክልል አካባቢዎች በሚንቀሳቀሰው ታጣቂ ቡድን ላይ የተጠናከረ ወታደራዊ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን የመንግሥት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ። የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ዛሬ ረፋድ በሰጡት መግለጫ፣ እራሱን የኦሮሞ ነጻነት ጦር ሲል የሚጠራውንና መንግሥት 'ሸኔ' ሲል በአሸባሪነት የፈረጀውን ታጣቂ ኃይል ለማስወገድ ፀረ ሽምቅ ውጊያ ኮማንዶ በማሰማራት ዘመቻ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል። ዘመቻው በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ እና በምሥራቅ ወለጋ፣ በምዕራብ እና በምሥራቅ ጉጂ፣ በሰሜን፣ በምሥራቅ እና በምዕራብ ሸዋ እንዲሁም በቦርና ዞኖች እየተካሄደ እንደሆነም ሚኒስትሩ ገልጸዋል። እየተደረገ ባለው ዘመቻ "በሺዎች የሚቆጠሩ" የታጣቂው ቡደኑ አባላት መገደላቸውን የገለጹት ሚኒስትሩ ፣ የቡድኑ አመራሮች፣ ታጣቂዎች፣ የስንቅና የሥልጠና ማዕከል "ከጥቅም ውጪ እንዲሆን ተደርጓል፤ መሳሪያዎችም ተማርከዋል ብለዋል። ለገሰ ቱሉ ( ዶ/ር) ታጣቂው ኃይል በተቀናጀው ኦፕሬሽን እየደረሰበት ያለውን ጉዳት መቋቋም ባለመቻሉ እየተበተነ ነው ሲሉም በመግለጫቸው አመልክተዋል። ሆኖም ከትናንት በስቲያ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ( ኦፌኮ) በሰጠው መግለጫ በኦሮሚያ ዞኖች ከዓለም ዓይን የተሰወረ ጦርነት እየተካሄደ ነው ሲል በጦርነቱ በርካታ ዜጎች በጅምላ መገደላቸውን ገልጿል። ኦፌኮ እየተፈጸሙ ነው ያላቸው "የጅምላ ግድያዎች"ም ገለልተኛ በሆነ ዓለም አቀፍ አካልም እንዲጣራ ጠይቋል። እንደ ፓርቲው መግለጫ ባለፉት ጥቂት ወራት ብቻ ንጹሃን ናቸው ያላቸው ከ297 በላይ ሰዎች በክልሉ በመንግሥት ኃይሎች ተገድለዋል፤ ከግማሽ ሚሊየን በላይ ሰዎችም ከቀያቸው ተፈናቅለዋል። የተባበሩት መንግሥታት የእርዳታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ( ኦቻ) በዚህ ሳምንት ባወጣው ሪፖርት በክልሉ ባለው የጸጥታ ችግር እና ግጭቶች ከግማሽ ሚሊየን በላይ ሰዎች ቀያቸውን ለቀው እንደወጡ አመልክቷል። ቀደም ብሎም መንግሥት በዘመቻው ድል እየቀናኝ ነው ማለቱን ተከትሎ ፣ ታጣቂ ቡድኑ በታጣቂዎቹ ላይ የደረሰ ጉዳት እንደሌለና የመንግሥት እርምጃ ሰላማዊ ሰዎች ላይ ጉዳት እያደረሰ መሆኑን በቃል አቀባዩ በኩል ለቢቢሲ ገልጾ ነበር። በክልሉ በታጣቂ ቡድኑና በመንግሥት መካከል እየተደረገ ባለው ውጊያ ሰላማዊ ሰዎች ሰለባ መሆናቸውን የአካባቢው ነዋሪዎችና ባለሥልጣናትም ለቢቢሲ ተናግረዋል። ነዋሪዎቹ ለቢቢሲ እንደተናገሩት መንግሥት ታጣቂ ቡድኑ በስፋት በሚንቀሳቀስባቸው አካባቢዎችም በሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) ጥቃትም ፈጽሟል። መንግሥት ግን እነዚህን ክሶች ያጣጣላቸው ሲሆን ዘመቻው በክልሉ እየደረሰ ያለውን ሞት፣ መፈናቀልና የንብረት ውድመት ለማስቀረት የተጀመረ ነው ብሏል። ባለፉት ዓመታት በኦሮሚያ ክልል በተለይ በምዕራብ ኦሮሚያ እና ምዕራብ ሸዋ አካባቢዎች በተለያዩ ጊዜያት ታጣቂዎች ፈፀሙት በተባለ ጥቃት በርካታ ሰላማዊ ሰዎች ተገድለዋል፤ ከቤት ንብረታቸውም ተፈናቅለዋል። ለገሰ (ዶ/ር) ዛሬ በሰጡት መግለጫ፣ ይህንን "ዘመቻ ለማጠልሸት የሚጥሩ ኃይሎች አሉ" ያሉ ሲሆን፣ እነዚህ ኃይሎች መንግሥት በታጣቂ ኃይሎች ላይ እርምጃ መውሰድ ሲጀምር ንጹሃን ዜጎች በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ጉዳት እየደረሰባቸው ነው በሚል የሚጮሁ ናቸው" ሲሉ ማንነታቸውን ያልገለጿቸውን አካላት ከሰዋል። ይሁን እንጂ ለተከታታይ ሳምንታት እየተካሄደ ባለው ዘመቻ በኦሮሚያ ክልል የሚኖሩ የሕብረተሰብ ክፍሎች "እፎይታ እየተሰማቸው ነው" ብለዋል። በመግለጫው የተነሱ ሌሎች ጉዳዮችስ ? ስለጎንደሩ ግጭት በጎንደር በቀብር ስፍራ በተወሰኑ ሰዎች አለመግባባት በተፈጠረ ግጭት ጉዳት ቢከሰትም ታቅዶ ነበር ያሉት 'ሴራ' መክሸፉን ሚኒስትሩ በመግለጫቸው ተናግረዋል። በግጭቱ የወደሙ መስጊዶችና አብያተ ክርስቲያናትን በጋራ ለመገንባት፣ ንብረታቸው የወደመባቸውና የተዘረፈባቸውን ግለሰቦች መልሶ ለማቋቋምም እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህ ግጭት እጃቸው እንዳለበት የተጠረጠሩ አካላትም ጉዳያቸው ፍርድ ቤት ቀርቦ እየታየ ነው ብለዋል። ከሳምንታት በፊት በጎንደር በቀብር ሥፍራ ላይ በተከሰተ ሃይማኖታዊ መልክ ያለው ግጭት ቢያንስ የ21 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ ከ150 በላይ ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱ መገለጹ ይታወሳል። ይህ ግጭት ወደ ሌሎች አካባቢዎች ተዛምቶም በስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ አብያተ ክርስቲያናት ተቃጥለዋል። ሚኒስትሩ ይህንን በተመለከተ የፌደራል ፖሊስ የመርማሪ ቡድን እስካሁን የተሰሩ ሥራዎችን በቅርቡ ለሕዝብ ይፋ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። 'አልሸባብ' የኮሚዩኒኬሽ አገልግሎት ሚኒስትሩ በመግለጫቸው የአልሻባብ የሽብር ቡድን ከሸኔ እና ከህወሓት ጋር በመቀናጀት በመሃል አገር፣ በምሥራቅና በምዕራብ የአገሪቱ ክፍሎች የሽብር ጥቃቶችን ለመፈፀም የወጠኑትን እቅድ መንግሥት በወሰደው እርምጃ ሳይሳካ መቅረቱን ተናግረዋል። በተወሰደው እርምጃም ቀደም ብሎ በርካታ ተጠርጣሪዎች መያዛቸውን ያስታወሱት ሚኒስትሩ፣ ባለፉት ቀናት በሶማሌ ክልል የተለያዩ ዞኖች፣ በኦሮሚያ፣ በምዕራብ ሐረርጌ እና በአርሲ፣ በምዕራብና ምሥራቅ ባሌ በርካታ የሽብር ቡድኑ አባላት በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ገልጸዋል። እስካሁንም 45 ተጠርጣሪዎች መያዛቸውን ሚኒስትሩ ገልጸው፣ ከተጠርጣሪዎቹ ጋር በርካታ የጦር መሣሪያዎች መያዛቸውንና በየቤተ እምነቶች የተቀበሩ መሣሪያዎችም በሕዝብ ጥቆማ እየተለቀሙ ነው ብለዋል። በዚህም 105 ክላሽንኮቭ ጠመንጃ፣ 13 ብሬል፣ 25 አርፒጂ፣ 25 ሳጥን የተለያዩ መጠን ያላቸው ጥይቶች፣ አራት ስናይፐር መሣሪያዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ሚኒስትሩ በመግለጫቸው አመልክተዋል። በአማራ ክልል ስላለው የፀጥታ ሁኔታ የአማራ ክልል እና አጎራባች ክልሎችን ለማጋጨት እና ሕገ ወጥነት ለማስፋፋት ሆነ ብለው የሚሰሩ ኃይሎች ላይ የሚወሰድ እርምጃ ተጠናክሮ መቀጠሉን ሚኒስትሩ ገልጸዋል። ከዚህም በተጨማሪ በክልሉ ውስጥ ያሉ "ኢ መደበኛ አደረጃጀቶች" ሕግ በማስከበርና ክልሉን ወደ ተረጋጋ ሁኔታ ለመመለስ አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ የሚያስችል አሰራር ተነድፎ አሳታፊ ውይይቶች እየተደረጉ መሆኑን ጠቁመዋል። ሚኒስትሩ አክለውም በክልሉ ላይ ሊቃጣ የሚችልን ማንኛውም ጥቃት ለመመከት የሚደረግ እንቅስቃሴ ለመግታት የሚሰሩ ኃይሎች ላይም ምህረት እንደማይኖር አስጠንቅቀዋል። ሰብዓዊ እርዳታ ለትግራይ ሚኒስትሩ ከሰሜኑ የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት ጋር በተያያዘም ወደ ትግራይ በየብስም፣ በአየርም የሚጓጓዘው ሰብዓዊ እርዳታ እንደቀጠለ መሆኑን ገልጸዋል። እንደ ሚኒስትሩ መግለጫ ከሆነ ባለፈው ሳምንት 165 ሰብዓዊ እርዳታ የጫኑ ተሽከርካሪዎች መቀለ ገብተዋል። የእርዳታ አቅራቢ ድርጅቶች ማቅረብ የሚችሉት እርዳታ ያህል እንዲያቀርቡ መንግሥትም የተቻለውን እያደረገ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፣ ነገር ግን የትግራይ ኃይሎች ለእርዳታ ማጓጓዝ ሥራው እንቅፋት ሆነዋል ብለዋል። "ህወሓት ከአፋር ክልል መውጣቱን ቢገልጽም፣ አሁንም በአፋር ክልል ከበርሃሌ፣ ከኮነባ፣ ከአብአላ እና ከመጋሌ ወረዳዎች አልወጣም። በአማራ ክልልም፣ አድርቃይ፣ ጠለምት፣ አበርገሌ እና ሌሎች አካባቢዎችን ይዞ ይገኛል" ሲሉ ከሰዋል። ህወሓት የሰብዓዊ እርዳታ ያለገደብ ትግራይ እንዲደርስ ሙሉ በሙሉ ከአፋር ክልል መውጣቱን ያስታወቀ ቢሆንም የክልሉ የፀጥታ ባለሥልጣናት ኃይሎቹ አሁንም በክልሉ እንደሚገኙ ለቢቢሲ መግለጻቸው የሚታወስ ነው። መንግሥት ከህወሓት የሚቃጣን ጥቃት ለመመከት በየትኛውም ጊዜና ሰዓት ሙሉ ዝግጁነትና አቅም ያለው መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፣ ግጭት ቀስቃሽ በሆኑ የማኅበራዊ ሚዲያ ዘመቻዎች ተነሳስቶ ወደ ግጭት እንደማይገባ ግን በአጽንኦት ተናግረዋል። የዋጋ ግሽበት በኢትዮጵያ የምግብ ዋጋ ንረትና ነዳጅ ዋጋ ጭማሪ አሳሳቢ ሆኗል። ሚኒስትሩ ዛሬ በሰጡት መግለጫም የሸቀጦች ዋጋ ግሽበት ከምርት አቅርቦት ጋር የሚያያዝ መሆኑን ጠቅሰው፣ ስኳር፣ ዘይት፣ የህጻናት አልሚ ምግቦች እና ሌሎች ምግብ ነክ ፍጆታዎችን በፍራንኮ ቫሉታ አገር ውስጥ እንዲገቡ ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል። ፍራንኮ ቫሉታ ሕጋዊ ከሆነ ምንጭ የሚገኝ የውጭ ምንዛሬ ሲሆን የባንክ ቤት ፈቃድ ሳያስፈልገው ከውጪ አገር ዕቃ ለማስገባት የሚያስችል ፈቃድ ነው። ባለፉት ወራት በ700 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ በመስኖ የለማ ስንዴ ውጤት በማስገኘቱ ከ25 ሚሊየን ኩንታል በላይ ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅ እና ተጨማሪ ምርት ለማግኘት ጥረት እየተደረገ እንደሆነም ሚኒስትሩ አክለዋል። ከዚህ ባሻገርም በግንባታው ዘርፍ ላይ እና በሲሚንቶ ላይ የሚታየውን ችግር ለመፍታትም እየተሠራ ነው ብለዋል።
|
https://www.bbc.com/amharic/news-61435712
|
business
|
‘ፓትሪዮት’፡ አሜሪካ ለዩክሬን የምትሰጣት ብዙ የተነገረለት አየር መቃወሚያ
|
ፕሬዝዳንት ዜሌንስኪ ምዕራባዊያንን አጥብቀው ሲጠይቁ የነበረው አንድ ነገር የአየር መቃወሚያ እንዲሰጣቸው ነበር። ምክንያቱም ሩሲያ በአየር ኃይሏ ኪዬቭን ጨምሮ ዋና ዋና ከተሞችን በጨለማ እንዲዋጡ አድርጋለች። በካሚካዚ ድሮንና በተወንጫፊ ሚሳኤሎች ብዙ ጥፋት አድርሳለች። ውሃና መብራት ለሚሊዮኖች ቅንጦት ሆኖ እንዲሰማቸው ሆኗል። ዩክሬናውያን የውርጩን ዘመን ያለማሞቅያ በብርድ እየተንዘፈዘፉ እንዲኖሩ ተደርገዋል። በዩክሬን ብዙ ከተሞች መብራት በፈረቃ ነው የሚከፋፈለው። ከዚህም የከፋ ጉዳት እንዳይደርስ በዩክሬን ሰማይ ላይ የሚፈነጩትን ድሮኖችና ሚሳኤሎች ጭጭ ማድረግ አስፈላጊ ሆኗል። አንድ ነገር መደረግ ነበረበት። ዜሌንስኪ ምዕራባዊያን ድረሱልን አሉ። ይነስም ይብዛ ደርሰውላቸዋል። ይሁንና እስከዛሬ የደረሳቸው የአየር መቃወሚያ ዘመናዊ ቢሆንም ከሩሲያ አቅም አንጻር ሲታይ የልብ አያደርስም። ፕሬዝዳንት ዜሌንስኪ ወደ አሜሪካ ማማተር ጀመሩ። ጆ ባይደን አላሳፈሯቸውም። ባይደን ለዜሌንስኪ አንድ ያረጋገጡላቸው ነገር ቢኖር ከሰሞኑ እጅግ የላቁ ናቸው የሚባሉትን የአየር መቃወሚያዎች እንደሚልኩላቸው ነው። ፓትሪዮት ይባላል ስማቸው። ይህ እርዳታ አሜሪካ ለዩክሬን 66 ቢሊዮን ዶላር ከለገሰች በኋላ የመጣ ትልቁ ስጦታ ሆኗል። ፓትሪዮት የአየር መቃወሚያዎች ውድ፣ በጣም ውጤታማ እና የልብ አድርስ ናቸው ይባላል። አንድ ፓትሪዮት ሚሳኤል ዋጋው ይጠራ ከተባለ ዋጋው 3 ሚሊዮን ዶላር ይደርሳል። ይህ ማለት በምሕጻረ ቃል ኤንኤኤምኤስ (NASAMS) የሚባሉትን ዘመናዊ የአየር መቃወሚያዎች በሦስት እጥፍ በዋጋ ይበልጣቸዋል። ፓትሪዮት ሚሳኤሎች የተሠሩት በኢራቅ ጦርነት ጊዜ ነበር፤ የሩሲያ ሠራሽ ሚሳኤሎችን ለመቃወም። ይህም እንደ አውሮፓዊያኑ በ1980ዎቹ መጀመርያ ማለት ነው። ነገር ግን ከዚያ ወዲህ ብዙ ማሻሻያዎች ተደርገውለት አሁን ወደደረሰበት ወደ ላቀ ደረጃ ደርሷል። ብዙ ያደጉ አገሮች አየር ክልላቸውን የሚጠብቁት በዚህ የአየር መቃወሚያ ነው። በቀላሉ ከቦታ ቦታ ማንቀሳቀስ ይቻላል። በአንድ ጊዜ በርካታ የአየር ጥቃቶችን መመከት ይችላል። የኤሌክትሮኒክ የግንኙነት እቀባ (ጃሚንግ) ቢሰነዘርበት ራሱ ይህን መመከት የሚያስችል መሣሪያ ተገጥሞለታል። 24 ሰዓት የራዳር ቅኝት ያደርጋል። ፓትሪዮት የአየር መቃወሚያዎችን ለመጠቀም የራዳር ጣቢያ፣ የዕዝ ጣቢያና ማስወንጨፊያ ማማ ያስፈልጋሉ። ከ40-160 ኪሎ ሜትር የጠላት ዒላማን ተምዘግዝገው ማደባየት ይችላሉ። በዋናነት አገልግሎታቸው የዋርዲያ ነው። ጥበቃ የማድረግ። ከተማን፣ ወይም አንድ አካባቢን፣ ወይም አንድ ግዙፍ መሠረተ ልማትን ከየትኛውም ዓይነት የአየር ጥቃት መጠበቅ። አሜሪካዊያን ወይም የኔቶ አባል አገራት ዩክሬን ገብተው እነዚህን መሣሪያዎች መጠቀም አይችሉም። ስለዚህ ዩክሬናዊያን ለዚሁ ፓትሪዮት የአየር መቃወሚያ ሚሳኤል ሲባል ልዩ ስልጠና መውሰድ ነበረባቸው። አሜሪካ በጀርመን ባላት የጦር ሰፈር ይህንኑ ሥልጠና ለተመረጡ ዩክሬናዊያን ሰጥታቸዋለች ተብሏል። ዛሬ ሐሙስ ሞስኮ ባወጣችው መግለጫ ፓትሪዮት የአየር መቃወሚያን ለዩክሬን ማስታጠቅ “የምዕራባዊያን ጠብ አጫሪነት” መቀጠሉን ማሳያ ነው ስትል ድርጊቱን አውግዛለች። ከዛሬ ጀምሮ እነዚህ መሣሪያዎች ዋንኛ ዒላማዋ እንደሚሆኑም ዝታለች። የጦር ባለሙያዎች ይህን ፓትሪዮት የአየር መቃወሚያ ለዩክሬን ከተሰጡ ስጦታዎች ትልቁ ብለው ያወድሱታል። ምክንያት ሲጠቅሱም በተለይ ኼርሶን ከተማን የዩክሬን ወታደሮች ከሩሲያ ወታደሮች ከነጠቁ በኋላ የዩክሬን ሰማይ ክፍት ሆኖ መቆየቱን ያወሳሉ። በዚህ የተነሳ ቁልፍ መሠረተ ልማቶች ክፉኛ ውድመት ሲደርስባቸው ቆይቷል። የዕለት ተዕለት ኑሮ በዩክሬን ፈተና የሆነውም ለዚሁ ነው። ይህም ሊሆን የቻለው የሩሲያ ሚሳኤሎችንና ድሮኖችን ማቆም የሚችል ቴክኖሎጂ በመጥፋቱ ነበር። አሁን ፓትሪዮት እንደ ስሙ አርበኝነቱን ያሳይ ይሆናል።
|
https://www.bbc.com/amharic/articles/c3g43d1n4dko
|
politics
|
ሩሲያ እና ዩክሬን: ሩሲያ ከአፍሪካ ጋር የጠበቀ ግንኙነት እንዴት ፈጠረች?
|
ሩሲያ በቅርብ አመታት በአፍሪካ ተጽዕኖዋን እያሰፋች ነው። ከዩክሬን ወረራ በኋላ አዳዲሶቹ አጋሮቿ ድጋፍ እንዲሰጧት ወይም እንደተባበሩት መንግሥታት ባሉ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ቢያንስ ገለልተኛ ሆነው እንዲቆዩ ትጠብቃለች። ከሊቢያ እስከ ማሊ፣ ሱዳን፣ መካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ በሞዛምቢክ እና ሌሎችም ሃገራት ሩሲያ ይበልጥ እየተሳተፈች ነው። አብዛኛው ተሳትፎዋ ደግሞ በወታደራዊ ኃይል ሲሆን አማፂያንን ወይም የጂሃዲስት ታጣቂዎችን መዋጋትን ይጨምራል። ኬንያ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ አባል ባትሆንም ሩስያ በዩክሬን የወሰደችውን እርምጃ አስመልክቶ ተቃውሞዋን በግልፅ አሳይታለች። ይህን የኬንያን አቋም የሚደግፉ ሌሎች ሃገራት ግን ብዙም አልታዩም። የአፍሪካ ህብረት ግጭቱ "እጅግ እንዳሳሰበው" ቢገልጽም በሩሲያ ላይ የሰነዘረው ትችት የለም። በብሪክስ ቡድን ውስጥ የሩሲያ አጋር የሆነችው ደቡብ አፍሪካ ሃገሪቱ ጦሯን ከዩክሬን እንድታስወጣ ስትጠይቅ በድርድር መፍትሄ እንዳለም ጨምራ ገልጻለች። ሩሲያ የዶኔስክ እና የሉሃንስክ ክልሎችን እንደ ገለልተኛ ሃገር ዕውቅና መስጠቷን እንደሚደግፉ የመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ፋውስቲን-አርቻንግ ቱዋዴራ መናገራቸው ተዘግቧል። ረቡዕ ደግሞ የሱዳኑ ምክትል መሪ መሃመድ ሃምዳን ዳጋሎ የልዑካን ቡድን እየመሩ ወደ ሞስኮ አቅንተዋል። ይህም በሁለቱ ሃገራት መካከል ያለውን የጠበቀ ግንኙነት ያሳያል። በአፍሪካ ያለው አጋርነት እየተቀየረ ስለመሆኑ ከሚያሳዩት ምሳሌዎች አንዱ ሩሲያ በዩክሬን ላይ ጥቃት ከመሰንዘሯ ከአንድ ሳምንት በፊት ፈረንሳይ በማሊ ጂሃዲስቶችን በመዋጋት ላይ የነበራት ተሳትፎ ማብቃቱ ነው። የማሊው ጠቅላይ ሚኒስትር ቾጌል ማይጋ ከፍራንስ 24 ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ሃገራቸው ከሩሲያ ጋር ወታደራዊ ስምምነቶች መፈራረሟን አረጋግጠዋል። አወዛጋቢው የሩሲያ የግል ወታደራዊ ኩባንያ ዋግነር ግሩፕ እጁ እንደሌለበትም ገልጸዋል። ይህ ለማሊ የሚደረገው የሩስያ እርዳታ ለቡርኪናፋሶ ወታደራዊ መንግሥት ከቀረበው ድጋፍ ጋር ተደምሮ ባለፉት አምስት ዓመታት ሩሲያ ይፋዊ እና መደበኛ ባልሆነ መልኩ በአፍሪካ ላይ ያላትን ተጽዕኖ ለማሳደግ እርምጃዎችን እየወሰደች መሆኑን ያሳያል። የታደሰው የሩስያ-አፍሪካ ግንኙነት እየተጠናከረ መጥቶ እአአ በ2019 በደቡባዊ ሩሲያ ሶቺ ከተማ የተካሄደው የመሪዎች ጉባኤ ላይ ከ50 በላይ የሃገራት ልዑካን ሲሳተፉ 43ቱ ርዕሳነ ብሔሮች ናቸው። ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ለመሪዎቹ በወቅቱ ባደረጉት ንግግር የነፃነት እንቅስቃሴዎችን የመደገፍ ታሪክን ለመጠበቅ፣ ንግድ እና ኢንቨስትመንትን ለማሳደግ ቃል ገብተዋል። ሩሲያ ለበርካታ የአፍሪካ መንግሥታት ግልጽ ያልሆነ የፀጥታ ጥበቃ፣ በስልጠና፣ በስለላ፣ በመሳሪያ እንዲሁም የሩሲያ ቅጥረኞችን በአካባቢው ግጭቶች ውስጥ በማሳተፍም ትታወቃለች። ፑቲን እንዳመለከቱት ታሪካዊ ግንኙነቱ ከሩሲያ በፊት ከነበረችው የሶቪየት ህብረት (ዩኤስኤስአር) ዘመን ድረስ የሚሄድ ሲሆን በሩሲያ እና በአሜሪካ መካከል ካሉት በርካታ የውድድር ቦታዎች መካከል አንዷ አፍሪካ ነበረች። እአአ በ 1991 የሶቭየት ህብረት ስትፈራርስ ጀምሮ እስካለፉት ጥቂት ዓመታት ድረስ ሩሲያ የሽግግር ጊዜ ውስጥ እያለፈች የነበረ ሲሆን ከአፍሪካ ጋር ያላት ግንኙነትም ዋነኛ አጀንዳ አልነበረም ። በድጋሚ የልዕለ ኃያልነት ደረጃን እንደገና ማግኘት ለሩሲያ ፕሬዚዳንት የውጭ ፖሊሲ ቅድሚያ የሚሰጡት ሆነ። እአአ በ 2014 ሩሲያ የክሬሚያን ሰርጥ ወደ ግዛቷ መቀላቀሏን ተከትሎ ዓለም አቀፍ ማዕቀቦችን ማስተናገድ ብቻ ሳይሆን ከአሜሪካ እና ከአውሮፓ ህብረት ጋር ያላት ግንኙነት በከፍተኛ ደረጃ ተበላሽቷል። ከዓለም አቀፍ መገለል ስጋት ጋር በተያያዘ ሞስኮ አዳዲስ አጋሮችን መፈለግ ጀመረች። በሩሲያ ብሔራዊ የሳይንስ አካዳሚ የአፍሪካ ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር የሆኑት ኢሪና አብራሞቫ "በእገዳው ምክንያት ሩሲያ ወደ ውጭ ለሚላከው ምርቷ አዲስ ገበያ መፈለግ አለባት" ብለዋል። ሩሲያ የምትፈልገው ገበያ ብቻ አይደለም። እየጨመረ ያለውን ዓለም አቀፋዊ ተጽዕኖ ትፈልግ ነበር እአአ በ 2014 በሶሪያ የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ የተሳተፈችው ፕሬዚደንት በሽር አል አሳድን ደግፋ ምዕራባውያን እያደረጉ ያሉትን ትርምስ ለማጉላት እና ሩሲያ እንዴት ማስተካከል እንደምትችል ለማሳየት ነው። ከሶሪያ በኋላ ደግሞ ወደ አፍሪካ አህጉር አቀናች። በደቡብ አፍሪካ የኩዋዙሉ-ናታል ዩኒቨርሲቲ የክብር ፕሮፌሰር ኢሪና ፊላቶቫ እንደሚሉት ሩሲያ በአፍሪካ ውስጥ የነበራት ቁልፍ ተግባር እንደሶሪያ ሁሉ የምዕራባውያንን ተጽዕኖ ማቃለል ነበር። ለምሳሌ አውሮፓውያን በሳህል ያለውን የጂሃዲስት ስጋት መቆጣጠር እንዳልቻሉ ለማሳየት ፈልጋ ነበር። ይህንንም በአፍሪካ ውስጥ ለማሳካት ሁለት ፖሊሲ ተጠቀመች። የመጀመሪያው በአንዳንድ ሃገራት ይፋዊ ወታደራዊ ስልጠናዎችን መስጠት ሲሆን ሌላኛው ደግሞ መደበኛ ያልሆኑ እንደ ዋግነር ግሩፕ ያሉ ድርጅቶች ደግሞ በመዋጋት ጭምር እየተሳተፉ ነው። በ2017 ከዋግነር ግሩፕ የሩስያ ቅጥረኛ ገዳይ ቡድን የታየባት የመጀመሪያዋ አፍሪካዊት ሀገር የመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ ነበረች። በኋላም እነሱን ተከትሎ ኦፊሴላዊ የሩሲያ ወታደራዊ አማካሪዎች ቡድን ገባ። ዓላማቸው ፕሬዝደንት ቱዋዴራን በስልጣን እንዲቆዩ መርዳት ነበር። በቅጥረኞቹ የሚፈጸሙት የጭካኔ ወንጀሎች እየተለመደ መጣ። ሩሲያ ግን አንድም ዜጋዋ በጦር ወንጀሎች እና በሠላማዊ ሰዎች ላይ ጥቃት በመፈጸም ውስጥ እንዳልተሳተፉ በተደጋጋሚ ገልጻለች። የሩስያ ቅጥረኞች በሊቢያ፣ ሱዳን፣ ሞዛምቢክ እና ማሊ የተለያዩ በተለያዩ ደረጃዎችን ሲንቀሳቀሱ ቆይተዋል። ሌላው የአህጉሪቱ ጠቀሜታ እያደገ መሄዱን የሚያመለክተው አፍሪካ ለሩሲያ የጦር መሳሪያ ኢንዱስትሪ ዋና ገበያ መሆኗ ነው። ወደ አፍሪካ ከሚገባው የጦር መሳሪያ ግማሽ ያህሉ ከሩሲያ መሆኑን የሀገሪቱ የመንግስት የጦር መሳሪያ ላኪ ኤጀንሲ አስታውቋል። ዋና መሣሪያ ገዢዎች አልጄሪያ እና ግብፅ ናቸው። ናይጄሪያ፣ ታንዛኒያ እና ካሜሩንም አዲስ ደንበኞች ሆነዋል። በዲፕሎማሲው ግንባርም ለጠበቀው ግንኙነት የቀረበ ሽልማት አለ። አፍሪካ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ከሩብ በላይ ድምጽ ያላት ሲሆን በሌሎች ዓለም አቀፍ ጉዳይ ላይ ጠንካራ ድምጽ ልትሆን ትችላለች። በሞስኮ ከፍተኛ የኢኮኖሚክስ ትምህርት ቤት የታተመውና ስለ አፍሪካ እና ሩሲያ ትብብር የሚገልጸው የ 2021 ዘገባ እንደሚያመለክተው ከዚህ ቀደም የሩሲያ ድርጊትን በተመለከተ የአፍሪካ ሀገራት ገለልተኛ የመሆን አዝማሚያ አሳይተዋል።
|
https://www.bbc.com/amharic/news-60543495
|
politics
|
የፑቲንን አስተዳደር ሙስና የሚታገሉት የሩስያ ሴቶች
|
ወንዶች ጎልተው የወጡበትን የሩስያ ፖለቲካ ለመለወጥ ሙስናን የሚቃወሙ ሴቶች ቆርጠው ተነስተዋል። እነዚህ ሴቶች የለውጥ ተምሳሌት ተብለዋል። ከተቃዋሚው አሌክሲ ናቫልኒ ጋር ይሠራሉ። ናቫልኒ የጸረ ሙስና ንቅናቄን ማዕከል ያደረገው ኤፍቢኬ ፓርቲውን ለፓርላማ ምርጫ ሲያዘጋጅ የእነዚህ ሴቶች ሚና ጉልህ ነው። የሩስያ ፓርላማ ለፕሬዘዳንት ቭላድሚር ፑቲን ታማኝ ነው። አብላጫውን ቁጥር የያዙትም ወንዶች ናቸው። ከታህታይ ምክር ቤቱ የሴቶች ድርሻ 16% ሲሆን ከላዕላይ ምክር ቤቱ ደግሞ 17% መቀመጫ አላቸው። በናቫልኒ ፓርቲ ወንዶችም ሴቶችም ቁልፍ ሚና አላቸው። በንቅናቄው ጎልተው የወጡ ሴቶች እነማን እንደሆኑ እናስተዋውቃችሁ። ዩሊያ ናቫልኒያ እአአ በ2000 ከናቫልኒ ጋር ትዳር የመሠረተችው ዩሊያ ሕይወቷ ፖሊስ ጣቢያና ፍርድ ቤት በመመላለስ የተሞላ ሆኗል። ቤቷም በተደጋጋሚ ተበርብሯል። ቱርክ የተዋወቁት ጥንዶች ሁለቱም 44ኛ ዓመታቸውን ይዘዋል። ዩሊያ ያጠናችው ዓለም አቀፍ ግንኙነት ሲሆን፤ ባንክ ውስጥ ሠርታለች። ቤታቸው ሞስኮ ሲሆን፤ ሴት ልጃቸው ዳርያ አሜሪካ እየተማረች ነው። ዩሊያ አሁን ከመገናኛ ብዙኃንና ከመንግሥት ስለላ ሸሽታ ጀርመን ነች። በመላው ሩስያ እሷን የሚደግፉ ሴቶች ቀይ ለብሰው ፎቶ በመነሳት ኢንስታግራም ላይ ለጥፈዋል። ባለቤቷ የሁለት ዓመት ከስምንት ወር እስር ሲፈረድበት ቀይ ለብሳ ነበር ፍርድ ቤት የተገኘችው። የፋሽን ጋዜጠኛዋ ካይታ ፌዶሮቫ ይህንን በማስመልከት ቀይ ከለበሰች ወዲህ ነው ሌሎች ሴቶች ቀይ በማድረግ ድጋፋቸውን ማሳየት የጀመሩት። "አትዘኚ። የከፋ ነገር አይከሰትም" በማለት ነበር ባለቤቷ ናቫልኒ ከመታሰሩ በፊት የተሰናበታት። ወደ ፓለቲካ ተሳትፎ የገባችው ባለፈው ነሐሴ ባለቤቷ ተመርዞ ለሞት በተቃረበበት ወቅት ነበር። ባለቤቷ ከተመረዘ በኋላ ከሰርቢያ ወደ ጀርመን እንዲወሰድ የወሰነችው እሷ ነበረች። ከሰመመን ሲነቃ "ትራሴን ታስተካክልልኝ የነበረችው እሷ እንደነበረች አስታውሳለሁ። እስክትመጣ እጠብቃት ነበር" ብሏል ናቫልኒ። ባለቤቷ አገግሞ ከጀርመን ወደ ሩስያ ሲመለስ ታስሯል። እስሩን በመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ ካደረጉ አንዷ ደግሞ እሷ ነበረች። የባለቤቷን ጸረ ሙስና ተቃውሞ የምትደግፈው ዩሊያ፤ ሰልፍ ከወጣች በኋላ 270 ዶላር ተቀጥታለች። ሊቦቭ ሶቦል የ33 ዓመቷ ጠበቃ በናቫልኒ ቡድን ውስጥ ከሚታወቁ አንዷ ናት። አሁን በቁም እስር ላይ ትገኛለች። እሷና ሌሎችም የናቫልኒ ደጋፊዎች ከተቃውሞ ሰልፉ በኋላ ታስረዋል። ለመታሰራቸው ምክንያት የተባለው የኮቪድ-19 መከላከያ መርህን መጣስ ነው። ናቫልኒ ሙስናን የሚያጋልጥበትን የዩቲዩብ ገጽ ፕሮዲውስ የምታደርገው ሊቦቭ ናት። ገጹ በሚሊዮኖች የሚቆጡ ተከታዮች አሉት። እአአ በ2019 ባለሥልጣኖች ከሞስኮ የምርጫ ኮሚቴ ጎትተው ሲያስወጧት የሚያሳይ ቪድዮ ካሰራጨች ወዲህ ታዋቂነቷ ጨምሯል። ከዚያ በኋላ ለአንድ ወር የረሀብ አድማ አድርጋለች። እሷና ሌሎችም የግል እጩዎች በሞስኮ ከተማ አስተዳደር ምርጫ እንዳይሳተፉ ታግደዋል። መስከረም ላይ ለሩስያ ፓርላማ ምርጫ የመወዳደር እቅድ አላት። ከ2011 ጀምሮ በናቫልኒ የጸረ ሙስና ፕሮጀክት ውስጥ ሠርታለች። 2014 ላይ ሚሮሳለቫ የተባለች ልጅ የወለደች ሲሆን፤ በሥራዋ ምክንያት በ2016 ባለቤቷ ጥቃት እንደደረሰበት ትናገራለች። በጸረ ሙስና ንቅናቄ ምክንያት እሷም ናቫልኒም በተደጋጋሚ ክስ ተመስርቶባቸዋል። ከከሰሷቸው መካከል ዩቭጌኒ ፕሪጎዚን የተባለው ባለሀብት ይጠቀሳል። ለክሬምሊን ቅርብ የሆነው ባለጸጋው "የፑቲን ሼፍ" በሚል ይታወቃል። አንስቲዥያ ቫስሌይቫ ዶክተር ናት። በዚህ ወር ፖሊሶች ቤቷን ሲበረብሩ ችላ ብላቸው የቤትሆቨንን ሙዚቃ ስትጫወት የሚያሳይ ቪድዮ ተለቆ ዝነኛ ሆናለች። የ36 ዓመቷ አንስቴዥያ ለናቫልኒ ቅርብ የሆነ የሀኪሞች ቡድን ትመራለች። 2017 ላይ ናቫልኒ አይኑ ላይ ጉዳት ሲደርስበት እሷ ነበረች ያከመችው። የሁለት ልጆች እናት ስትሆን፤ ናቫልኒን የሚደግፍ ሰልፍ በማካሄዷ የቁም እስር ላይ ትገኛለች። ከዚህ ቀደም ከሞስኮ ታይምስ ጋር ባደረገችው ቃለ ምልልስ የሩስያ መንግሥት ለኮሮናቫይረስ የሰጠውን ምላሽ ተችታለች። እናቷ ሀኪም እንደነበሩና የፖለቲካ ተሳትፎ ለማዳበር የተነሳሳችውም በዚህ ምክንያት እንደሆነ ትናገራለች። "የአገራችን ጤና ሥርዓት ውስጥ ያለውን እያዩ ፖለቲካ ውስጥ አለመሳተፍ አይቻልም" ትላለች። ኪራ ያርሚሽ ከ2014 ጀምሮ የናቫልኒ ቃል አቀባይ ስትሆን፤ በቁም እስር ላይ ትገኛለች። ወደተለያዩ አገሮች ሲጓዝ አብራው ትሄዳለች። ነሐሴ ላይ አውሮፕላን ውስጥ ሳለ ተመርዞ ራሱን ሲስትም አብረው እየተጓዙ ነበር። የሞስኮ ዓለም አቀፍ ተቋምን የተቀላቀለችው የቴሌቭዥን የተሰጥኦ ውድድር አሸንፋ ሲሆን፤ ያጠናችው ጋዜጠኝነት ነው። በጸረ ሙስና ንቅናቄ ከታሰረች በኋላ በማረሚያ ቤት ስለሚገኙ ሴቶች የሚያትት ረዥም ልቦለድ ጽፋለች። በናቫልኒ የዩቲዩብ ገጽም ብዙ መሰናዶዎች መርታለች። ኦልጋ ሚካሎቫ የናቫልኒ ጠበቃ ናት። በአውሮፓ የሰብዓዊ መብቶች ፍርድ ቤት ልምድ አላት። 2017 ላይ ሩስያ ናቫልኒን እና ወንድሙን ገንዘብ አጭበርብራችኋላ ብላ ከሳ ነበር። ፍርድ ቤቱ ግን ክሱን ውድቅ አድርጎ የሩስያ የፍትሕ ሚንስትር በሺዎች የሚቆጠር ዶላር ካሳ እንዲከፍል ወስኗል። ናቫልኒ ከጀርመን ወደ ሩስያ ሲመለስ በቁጥጥር ሥር የዋለው ከዚህ ክስ ጋር በተያያዘ ነው። ኢኮ ሞስኪቭ ከተባለ የራድዮ ጣቢያ ጋር ባደረገችው ቆይታ ሕገ አውጪውና ሕግ አስፈጻሚው መካከል ልዩነት የለም ስትል ተችታለች። የአውሮፓ ትልቁ የሰብዓዊ መብት ፍርድ ቤት በሆነው ካውንስል ውስጥ ለናቫልኒ ጥብቅና የምትቆመውም ኦልጋ ናት።
|
https://www.bbc.com/amharic/56066793
|
health
|
ለ15 ወራት ደሞዛቸው ያልተከፈላቸው የትግራይ የሕክምና ባለሙያዎች
|
የፌደራል መንግሥቱ እና የትግራይ ኃይሎች ወደ ጦርነት ከመግባታቸው በፊት ማጀታቸው የሞላ፣ ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት የሚልኩ፣ ለቤተሰቦቻቸው እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው የሚተርፉ ነበሩ። በመቀለ የሚገኙ እና ቢቢሲ ያነጋገራቸው መምህራን፣ የሕክምና ባለሙያዎች እና ሌሎች የመንግሥት ተቀጣሪዎች ከሁለት ዓመት በፊት የነበራቸው ሕይወት የዛሬውን አይመስልም ነበር። ዛሬ በትግራይ ያለው ጦርነት ተባብሶ፣ በክልሉ የማኅበራዊ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ሥራ አቁመው፣ የሰብዓዊ እርዳታ ተመናምኖ ሁሉም የሰው እጅ ጠባቂ እንደሆነ ይናገራሉ። ለሌሎች ይዘረጋ የነበረ እጅ ዛሬ ለምጽዋት ደጅ ይጠናል። ለገባ ለወጣ ይቆረስበት የነበረ መሶብ ጦሙን አድሯል። ዕድለኛ የሆነ 15 ኪሎ ግራም የእርዳታ ስንዴ ዱቄት ተቀብሎ ልጆቹን ያበላል። የተቀረው እና ምንም ማድረግ የማይችለው ደግሞ የተሻለ ቀን እንዲመጣ፣ ጦርነቱ እንዲያበቃና ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ይጸልያል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ኅብረት እና አሜሪካ እየተባባሰ የመጣው ከባድ ውጊያ ያለውን ሁኔታ አስከፊ ሊያደርገው እንደሚችል በመግለጽ ማስጠንቀቃቸው ይታወሳል። ወደ ትግራይ ክልል ጋዜጠኞች እንዲገቡ ባለመፍቀዱ እና ማኅበራዊ አገልግሎቶች በመቋረጣቸው ምክንያት፣ የግጭቱ መጠን እና ያስከተለው ሰብአዊ ቀውስ ስፋት በዝርዝር ለመረዳት አስቸጋሪ አድርጎታል። ቢቢሲ ያነጋገራቸውን የሕክምና ባለሙያዎች ሕይወት እናንተ ቤት ምን ይመስላል ሲል ጠይቋቸዋል። በአይደር ሆስፒታል የቀዶ ጥገና ባለሞያ የሆኑት ዶ/ር ፋሲካ ዓምደሥላሴ ለረዥም ወራት ደሞዝ እንዳልተቀበሉ እና ከብዙ ወራት በኋላ “ዕድል ቀንቶ” የሰብአዊ እርዳታ ድርጅቶች የሚሰጡትን የእርዳታ ስንዴ መቀበላቸውን ይናገራሉ። “ሕይወት አድን ምግብ ካላገኙ በሚሊዮን ከሚቆጠሩ ህጻናት ጋር ሲነጻጸር ልጆቼ ዕድለኞች ናቸው” በማለት ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ማኅበር የሰጣቸውን እርዳታ የሚያሳይ ምስልና ጽሑፍ በትዊተር ገጻቸው ላይም አስፍረው ነበር። “እርዳታ ሳገኝ በጣም ተደሰትኩ፤ ከዚህ የባሰ መጥፋት፣ ህመም እና ሞት ነው የሚመጣው። በርካታ መልካም ሕይወት የነበራቸው ሰዎች፣ አስተማሪዎች . . . ወደ ጎዳና ወጥተው እያየናቸው ነው። የጉልበት ሥራ የሚሰሩ፣ መንገድ ላይ ሳሙና የሚሸጡ ብዙ የመንግሥት ሠራተኞች አሉ” ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል። የሆስፒታሉ ሠራተኞች በግንቦት ወር 2013 ዓ.ም. መጨረሻ ላይ ደሞዛቸው እንደተከፈላቸው ገልፀው፣ ነገር ግን በዚያው ዓመት ሰኔ ወር ላይ የትግራይ ኃይሎች ከተማዋን ከተቆጣጠሩ በኋላ የወር ደሞዛቸው አልተከፈላቸውም። ዶ/ር ፋሲካ፣ አክለውም በባሕር ማዶ ወዳጅ ዘመድ ያላቸው የእነርሱን ድጋፍ እየጠበቁ አንደሚኖሩ አስታውሰው፣ ነገር ግን ሁሉም የሚደግፈው ዘመድ አለው ማለት እንዳልሆነ ያብራራሉ። አክለውም “በሰብአዊ እርዳታ የሚመጣው ስንዴ ተቀብለው ለወፍጮ ቤት የሚሆን ገንዘብ የሚቸገሩ አሉ” ሲሉ የችግሩን ግዝፈት ለማሳየት ይጥራሉ። በአይደር ሆስፒታል ድንገተኛ ክፍል ውስጥ የሚሰራ እና ከሰኔ 30 ጀምሮ ወርሃዊ ደሞዙን ያላገኘው ስሜን አትግለፁ ያለን ዶክተር “ባልደረቦቼ በሙሉ ችግር ውስጥ ናቸው” ይላል። ይህ ዶክተር ላለፉት ሦስት ዓመታት በሆስፒታሉ ውስጥ ያገለገለ ሲሆን፣ ባለትዳርና የአንድ ልጅ አባት ነው። “ከዚህ በፊት ሕይወቴን እየመራሁ ወላጆቼን ጭምር እረዳ ነበር። አሁን ግን ለአካለ መጠን እንዳልደረሰ ልጅ ተመልሰው ወላጆቼ እየረዱኝ ነው። እነሱ ገጠር ሆነው የሚያገኟትን እህል እየተካፈልን ነው የምንኖረው።” አብዛኛዎቹ የሆስፒታሉ ሠራተኞች እንደሌላው ማኅበረሰብ እርዳታ ይጠብቃሉ የምትለው ነርስ ፍሬ በበኩሏ፣ “ከገበሬ ዘመዶቼና ወዳጆቼ የሚላክልኝን እየጠበቅኩ ቀን እገፋለሁ” ትላለች። ከጦርነቱ በፊትም ቢሆን በክልሉ ውስጥ በነበሩ ማኅበራዊ ችግሮች እና ዝቅተኛ የሥራ ዕድል ምክንያት በርካታ የቤተሰብ አባላት እርስ በእርስ በመተጋገዝ ላይ ነበር የሚኖሩት። “የቤተሰብና የዘመድ ኃላፊነት የተሸከምን ዜጎች እንደመሆናችን መጠን ያለ ክፍያ ልጆችን ማሳደግ ከባድ ነው። ምግብ ተበልቶ በሕይወት መቆየት ከባድ ሆኖ ሳለ በህክምና ሥነ-ምግባር ስለ ሌሎች ሕይወት መጨነቅ ስላለብን፣ ሥራ መቋረጥ የለበትም በሚል በባዶ ሆዱ ወደ ሥራ ቦታ መጥቶ ነው እየሰራ ያለው” ስትል ነርስ ፍሬ ትገልጻለች። የመቀለ ዩኒቨርስቲ አካል የሆነው አይደር ሪፈራል ሆስፒታል በትምህርት ሚኒስቴር ስር የሚተዳደር ነው። ቢቢሲምለሠራተኞቹ የደመወዝ አልተከፈለንም ጥያቄ ምላሽ ለማግኘት ከትምህርት ሚኒስቴር እና ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በስልክና በጽሑፍ መልዕክት ብንሞክርም ጥረታችን አልተሳካም። በትግራይ ከአንድ ዓመት በላይ የባንክ እና የትራንስፖርት አገልግሎት የተቋረጠ ሲሆን መሠረታዊ ሸቀጦች ከአፋር እና ከአማራ ክልሎች "በሕገ-ወጥ" መንገድ እንደሚገቡ የቢቢሲ ምንጮች ገልጸዋል። በዚህም ምክንያት ከፍተኛ የመሠረታዊ ሸቀጦች የዋጋ ንረት እና የገንዘብ እጥረት እንዳለ፣ ካለው የነዳጅ እጥረት የተነሳም የትራንስፖርት ዋጋ በመናሩ የዕለት ኑሯቸው መክበዱን ነዋሪዎች ያስረዳሉ። “ለራስና ለልጆች መሆን አለመቻል ሕይወት ዓላማ እንዲያጣ ያደርጋል። በአሁኑ ጊዜ መኮረኒ፣ ሩዝ፣ ዘይት ውድ ናቸው” ሲሉ ሌላ ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ የሕክምና ባለሙያ ተናግረዋል። አብዛኞቹ የመንግሥት ሠራተኞች የሚኖሩት በኪራይ ቤት በመሆኑ፣ ገንዘብ አለማግኘት አከራይና ተከራይ ከፍተኛ ውጥረት ውስጥ እንዲገቡ አድርጓል የሚለው ደግሞ በመቀለ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ መምህርና የጤና ባለሙያ የሆነው ዶክተር ነው። “አብዛኛው ሠራተኛ አይደለም ለቤት ኪራይ ለታክሲም መክፈል አይችልም። እኔ የሰው ፊት ላለማየት ስል የሞቀ ቤት ባይሆንም 70 ካሬ መንደር በሚገኘው ያላለቀ ቤት ውስጥ ነው የምኖረው። ኤሌክትሪክ እና ውሃ በጭራሽ አይታሰቡም፤ ከጉድጓድ የሚመጣ ውሃ ነው የምንጠጣው። ውሃ ማከሚያ መድኃኒት እንኳ አናገኝም።” የትግራይ ክልል ከአንድ ዓመት በላይ ከበባ ላይ በመቆየቱ ምክንያት የሕክምና ባለሞያዎች እና ታካሚዎች የሚያደርጉት ግራ ገብቷቸዋል የሚሉት አስተያየት ሰጪዎቹ፤ “የሰብአዊ እርዳታ እንዲሁም የመድኃኒት አቅርቦት እጥረት ተከትሎ በርካታ ታካሚዎች እጃችን ላይ እየሞቱ ይገኛሉ” ይላሉ። ህጻናት በምግብ እጥረት ዋነኛ ተጠቂዎች መሆናቸውን የገለፁት የሕክምና ባለሙያዎቹ፣ ካለፈው ዓመት ጀምሮ በትግራይ 2,500 የሚጠጉ ህጻናት በምግብ እጥረት መሞታቸውን ቢቢሲ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ይህ አኃዝ ግን መሬት ላይ ያለውን እውነታ እንደማያሳይ የህክምና ባለሙያዎች ያስረዳሉ። የሰብአዊ እርዳታ ሰጪ ተቋማት ጦርነቱ አስከፊ የሆነ ሰብአዊ ቀውስ ማስከተሉና በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ገድሎ ከሁለት ሚሊዮን በላይ ሰዎች አፈናቅሏል ሲሉ ይገልጻሉ። “ሁኔታው በጣም አሳሳቢ ከመሆኑ የተነሳ ደሞዛችን ሳይከፈለን መስራታችን ብቻ ሳይሆን ችግሩ ታካሚዎች ላይ ጭምር ሲታይ ከባድ ያደርገዋል። ተርበን መጥተንም የተራቡ ሰዎች ማከም፣ እንዲህ አይነት ምግብ ብሉ ማለት ይከብዳል። የምንሰራበት ሆስፒታል ሳይቀር የሚዘጋበት ደረጃ ላይ ደርሷል” ሲል ስሙ እንዳይጠቀስ የጠየቀው ዶክተር ተናግሯል። አክሎም “ብዙውን ጊዜ የምናሳልፈው በሥራ ላይ ነው፤ ባለን ጊዜ ደግሞ ዛሬ ወይም ነገ እርዳታ እናገኛለን ብለን ስንጠብቅ እንውላለን። ገጠር የሚኖሩ ወላጆቼ እርሻ ስላላቸው አሁን እየረዱኝ ነው” ብሏል። “በእግዚአብሔር ጸጋ ነው የምኖረው” የምትለው ነርስ ፍሬ፣ ከሰባት ዓመት በታች የሆኑ ህጻናት ልጆች እንዳሏትና ልጆቿ የለመዱት ምግብ እንድታቀርብላቸው ሲጠይቋት እንደምትጨነቅ ትናግራለች። “ምግብ ሳይበሉ የሚያድሩበት ጊዜም ስላለ፣ ለጥያቄያቸው መልስ ማጣት የሚፈጥረው ህመም ከባድ ነው። በጭንቀት ራሴን እንዳልጎዳ እፈራለሁ።” በሰኔ ወር መጀመሪያ 2022 የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ክብሮም ገብረሥላሴ ለቢቢሲ እንደተናገሩት በክልሉ ትልቁ ሆስፒታል በመብራት መቆራረጥ እና በመድኃኒት እጦት ምክንያት ተገቢውን አገልግሎት መስጠት አቁሟል ብለው ነበር። ነገር ግን በጦርነቱ ምክንያት በተፈጠሩ ተደራራቢ ችግሮች ምክንያት፣ ሆስፒታሉ የሚሰጠው የህክምና አገልግሎት የሚፈለገው ያህል ባይሆንም ሠራተኞች በግል ችግራቸው ምክንያት ሥራ ለማቆም አስበው አያውቁም ስትል ነርስ ፍሬ ገልጻለች። “መንግሥት ግዴታውን እንዳልተወጣ አውቃለሁ፤ ሆኖም እኔ ወደ ሥራ ገበታ ባለመምጣቴ የሚጠፋ ሕይወት አለ ብዬ ስለማስብ ነው ወደ ሥራ የምመጣው። እኛ አገልግሎት ካቆምን ነገ እዚህ አገር ማን ይኖራል? ብዙ ታማሚዎች በመድኃኒት፣ በምግብ እና በኦክሲጅን እጦት ሞተዋል። ነገር ግን ሊተርፍ የሚችለውን ሰው ማዳን በመቻሌ ውጤታማ ነኝ ብዬ አስባለሁ።” ዶ/ር ፋሲካ ዓምደሥላሴ ሕክምና ባለሙያዎቹ እየሰሩ የሚገኙበትን አስቸጋሪ ሁኔታ ሲያስረዱ “ቁርስ ሳይበሉ ወደ ሥራ ቦታ መጥተው የወደቁ ነርሶች አሉ፤ በጣም አሳዛኝ ሁኔታ ላይ ነን። አንድ ሰው ያመጣው ምግብም ቅመሺ ተብላ ልጆቼን ቁርስ ሳልሰጣቸው ነው የመጣሁት ብላ ያለቀሰች ነርስ አለች። በችግር ምክንያት የሚለምኑና ወደ ቤተሰቦቻቸው የተመለሱ አሉ” ይላሉ። “የምንኖረው ሕይወት፣ ይሆናል ብለን አስበነው የማናውቅ ነው” የሚለው ሌላው በሆስፒታሉ ውስጥ መምህርና የጤና ባለሙያ የሆነው ዶክተር በበኩሉ፣ በትራንስፖርት እና በገንዘብ ችግር ምክንያት ቤተሰቦቹ ያሉበት ሁኔታ እንደማያውቅ ይናገራል። “ሕይወታችን በቃላት ከሚገለጸው በላይ ነው፤ ነገር ግን ሥራ አላቆምንም። ለማንኛውም እኛ የምንሄደው መድኃኒት ቢያጡም ‘አይዟችሁ’ ለማለት ከታካሚዎች መራቅ ስለሌለብን ነው። ሙያችን ገንዘብ አልተከፈለንም በሚል የሚተው አይደለም። እዚህ የታመሙትን ትተን ቤት እንድንቀመጥ ህሊናችን አይፈቅድልንም። የተራቡትን ማብላት ባልችልም የታመሙትን መድኃኒቱን ሰጥቼ በሕይወት ማኖር እችላለሁ።” የሆስፒታሉ ሠራተኞች በፌደራል መንግሥት ተቋም ተቀጥረው የሚሰሩ በመሆናቸው በጦርነቱ ምክንያት “ሆን ተብሎ” የወር ደሞዛችን ተይዟል የሚል ቅሬታ አላቸው። “ብዙ የሰብአዊ እርዳታ ኤጀንሲዎች ገንዘብ አምጥተው ለሠራተኞቻቸው ይከፍላሉ፤ የቀጠረን አካል ግን ዝም አለ። ባንክ ዝግ ነው፤ ከዚህ በፊት የቆጠብኩት በችግር ጊዜ እንዳልጠቀምበት ጭምር ነው የተከለከልኩት። ይግባኝ የማይባል ፍርድ” በማለት አንድ ሠራተኛ ቅሬታውን ለቢቢሲ ገልጿል። እስከ አሁን ግጭቱን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የተደረጉ ጥረቶች አልተሳኩም። “በጣም የሚያሳስበኝ ነገር ይህ ሁኔታ መቼ እንደሚያበቃ ነው። ልጆቻችን ይዘን እንዳንወጣ የስደት መንገዱ በእግር የሚኬድ ስለሆነ በወታደሮች እንዳንገደል እንፈራለን። ሙሉ ለሙሉ ተከባችሁ በረሃብ ጥፉ የሚያስብል ሁኔታ ነው ያለው” ብሏል ዶክተሩ።
|
https://www.bbc.com/amharic/articles/cgegl7dd8k7o
|
sports
|
እግር ኳስ ፡ የዲያጎ ማራዶና የአስከሬን ምርመራ ውጤት ይፋ ሆነ
|
ከአንድ ወር በፊት በልብ ችግር ምክንያት ያረፈው የቀድሞው የዓለም የእግር ኳስ ኮከብ በዲያጎ አርማንዶ ማራዶና አስከሬን ላይ የተደረገው ምርምራ ይፋ ሆነ። የአርጀንቲናዊው የእግር ኳስ ኮከብ የአስከሬን ምርመራ እንዳረጋገጠው ህይወቱ ባለፈበት ጊዜ ምንም አይነት አልኮልም ሆነ ዕጽ መውሰዱን የሚያሳይ ምልክቶች እንዳልተገኙ ተገልጿል። በአውሮፓውያኑ 1986 ላይ በተደረገው የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ውድድር ላይ ኮከብ በመሆን አገሩ አርጀንቲና በአሸናፊነት ዋንጫ እንድትነሳ ያስቻለው ማራዶና በኅዳር ወር ላይ ነበር በድንገት ህይወቱ ያለፈው። ማራዶና በሞተበት ጊዜ ለህይወቱ ማለፍ በርካታ መላምቶች ሲቀርቡ የነበረ ሲሆን፤ በአስከሬኑ ላይ በተደረገው ምርመራ ተገኘው ውጤት ግን ከብዙዎች ግምት የተለየ ሆኗል። ምርመራው እንዳመለከው የ60 ዓመቱ ማራዶና በኩላሊቱ፣ በልቡ ላይና በሳምባው ላይ ችግሮች ነበሩበት ተብሏል። በእግር ኳስ ኮከቡ አስከሬን ላይ ምርመራ እንዲደረግ የታዘዘው በተለይ ማራዶና ህይወቱ ከማለፉ በፊት በተደረገለት የህክምና ድጋፍ ዙሪያ ለሞቱ ምክንያት ሊሆን የሚችል ማንኛውም አይነት ቸልተኝነት ከነበረ ለማጣራት ነበር። የምን ጊዜም የእግር ኳስ ኮከብ ተደርጎ የሚታሰበው ዲያጎ አርማንዶ ማራዶና ከጥቂት ሳምንታት በፊት በኅዳር ወር መጀመሪያ ላይ በአንጎሉ ውስጥ ላጋጠመው የደም መርጋት የተሳካ የቀዶ ህክምና ተደርጎለት የነበረ ሲሆን፤ በተጨማሪም ለነበረበት የአልኮል ሱስ ህክምና ለመጀመር እየተዘጋጀ ነበር። ከአገሩ አርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ባሻገር ለቦካ ጁኒየርስና ለናፖሊ ክለቦች የተጫወተው ማራዶና ህይወቱ ባለፈበት ዕለት በአስከሬኑ ላይ ምርመራ በተደረገበት ጊዜ በከባድ የልብ ችግር ምክንያት መሞቱን ለመወቅ ተችሎ ነበር። ከማራዶና ሞት ጋር በተያያዘ በመጨረሻው ሰዓት የህክምና ድጋፍ ያደረገለት ዶክተር ህይወቱን ለማዳን ተገቢውን ድጋፍ አላደረገም በሚሉና በሌሎችም ጉዳዮች ሲወቀስ የቆየ ቢሆንም በመጨረሻ የተገኘው የአስከሬን ምርመራ ውጤት ግን ነጻ ያወጣዋል ተብሏል። ከማራዶና ሞት በኋላ የሦስት ቀናት ብሔራዊ የሐዘን ቀናት በመላዋ አርጀንቲና ታውጆ አስከሬኑ በዋና ከተማዋ ቦነስ አይስ ውስጥ በሚገኘው የፕሬዝዳንቱ ቤተ መንግሥት ውስጥ ተቀምጦ፤ አገሬው በከፍተኛ ቁጥር በመገኘት ሐዘኑን በመግለጽ እንደተሰናበተው ይታወሳል። ይሁን እንጂ የማራዶና አስከሬን እስካሁን እንደተቀመጠ ይገኛል ለዚህም ምክንያቱ ከተደረገው ምርመራ ባሻገር ከማራዶና ሞት በኋላ ኮከቡን የእግር ኳስ ተጫዋች አባትነት የሚጠይቅ አቤቱታ ለፍርድ ቤት በመቅረቡ ነው። ለዚህም የአርጀንቲና አንድ ፍርድ ቤት የማራዶና አስከሬን ለዘረ መል (DNA) ምርመራ ስለሚፈለግ "ባለበት ይጠበቅ" የሚል በሰጠው ውሳኔ መሰረት አስከሬኑ ለጊዜው ቦነስ አይረስ ውስጥ በሚገኝ አንድ የግል የአስከሬን ማቆያ ውስጥ እንዲቆይ ተወስኗል።
|
https://www.bbc.com/amharic/news-55458658
|
health
|
በአፍሪካ የተፈራውን ያክል ድህነት ሰዎችን ለኮሮናቫይረስ አጋልጧል?
|
ከአፍሪካ በኮሮናቫይረስ በተያዙ ሰዎች ቁጥር ቀዳሚዋ ደቡብ አፍሪካ ናት። አሁን ላይ ግን በአገሪቱ በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር እየቀነሰ ነው። በሌሎች የአፍሪካ አገራት ያለው ስርጭት መጠንም በአንጻራዊነት ዝግ ያለ ነው። አፍሪካ ውስጥ በርካታ የተጨናነቁ መንደሮች አሉ። በእነዚህ መንደሮች ንጽህናና አካላዊ ርቀት መጠበቅ ከባድ ነው። በአንጻራዊነት ደህና በሚባሉ ከተማ ቀመስ አካባቢዎች የሚኖሩ ሰዎች ቫይረሱን በፍጥነት ሊያሰራጩት እንደሚችሉ የጤና ባለሙያዎች ሲያስጠነቅቁ ተደምጠዋል። በደቡብ አፍሪካ የኮቪድ-19 አማካሪ ቡድን ኃላፊ ሳሊም አብዱል ካሪም እንደሚሉት፤ ሰዎች በብዛት፣ ተጨናንቀው በሚኖሩባቸው አካባቢዎች ቫይረሱ በፍጥነት ይሰራጫል። እውነታው ከዚህ የባለሙያዎች መላ ምት ተቃራኒ ቢሆንስ? የተጨናነቁ መንደሮች እንደተገመተው ለበሽታው መሰራጨት ምክንያት ሳይሆኑ እንዲያውም ቫይረሱ በስፋት እንዳይስፋፋ አድርገው ቢሆንስ? የአህጉሪቱ ድህነት እንደተፈራው ለወረርሽኙ ተጋላጭ ሳያደርጋት ቀርቶ ቢሆንስ? ሚሥጥሩ ምንድን ነው? ኮሮናቫይረስ መሰራጨት ሲጀምር ሁሉም ባለሙያዎች አፍሪካ አደጋ ውስጥ ትወድቃለች ብለዋል። የደቡብ አፍሪካው ቫይሮሎጂስት ሻቢር ማህዲ “ከፍተኛ ችግር ውስጥ እንደምንገባ አስቤ ነበር። አበቃልን ብዬም ነበር” ይላሉ። በጣም ተስፋ ሰጪ ናቸው የተባሉ መላ ምቶች ሳይቀሩ ለህሙማን አልጋ እንደሚጠፋ፣ የጤና ሥርዓቱ እንደሚቃወስ ሲጠቁሙ ነበር። ሆኖም ግን በደቡብ አፍሪካ በቫይረሱ ሳቢያ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከዩናይትድ ኪንግደም በሰባት እጥፍ ያንሳል። ደቡብ አፍሪካ ብቻ ሳትሆን ሌሎች አገራትም የተፈራው ያህል ቫይረሱ ጉዳት እያደረሰባቸው አይደለም። ሆስፒታሎች እንደተሰጋው አልተጨናነቁም። በተቀረው ዓለም እንደተከሰተው የቫይረሱ ስርጭት በከፍተኛ ሁኔታ ጫፍ ላይ ደርሶም አልታየም። ፕ/ር ሻቢር፤ “በአብዛኞቹ የአፍሪካ አገራት የቫይረሱ ስርጭት ጫፍ አልታየም። ለምን እንደሆነ አልገባኝም። ግልጽ ያልሆነና ለማመን የሚያስቸግር ነው” ይላሉ። አፍሪካ ውስጥ ኮሮናቫይረስ በአስጊ ሁኔታ ያልተሰራጨው አብዛኛው የአህጉሪቱ ነዋሪ ወጣት ስለሆነ ነው የሚሉ ባለሙያዎች አሉ። የአፍሪካውያን አማካይ እድሜ ከአውሮፓውያኑ በግማሽ ያንሳል። የቶኒ ብሌር ተቋም የአፍሪካ ዳይሬክተር ቲም ብሮምፊልድ እንደሚሉት፤ አፍሪካ የወጣቶች አህጉር መሆኗ ከበሽታው ተከላክሏታል። ነገር ግን በበሽታው የተያዙ ሰዎችን እድሜ ከግምት ያስገቡ የስታትስቲክስ መረጃዎች እንደሚያሳዩት፤ እድሜ ከበሽታው የሚከላከል ብቸኛ ነገር አይደለም። ፕ/ር ሳሊም “ትልቁ ነጥብ እድሜ አይደለም” የሚሉትም ለዚህ ነው። በደቡብ አፍሪካ እና በሌሎችም አገራት ወረርሽኙ መሰራጨት እንደጀመረ የእንቅስቃሴ ገደብ መጣሉ ሚናው ቀላል አይደለም። ሰዎች የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል እንዲያደርጉም ጠንካራ ማስጠንቀቂያ ተላልፏል። በሌላ በኩል የአህጉሪቱ ከፍታ እና ሙቀት የበሽታውን ስርጭት ይቀንሳል የሚለው መላ ምት እንደማይሠራ ተገልጿል። በቂ የመሠረተ ልማት ዝርጋት ባለመኖሩ ለወደፊት በበሽታው የሚያዙ ሰዎች ቁጥር ሊጨምር ይችላል የሚል ስጋት ያላቸው አሉ። “አፍሪካ ክፉውን ጊዜ አልፋለች ማለት አልችልም። አንድ ቀን ወረርሽኙ በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምር ይሆናል” ሲሉ ፕ/ር ሳሊም ያስረዳሉ። ሌሎቹ ኮሮናቫይረሶች በሶዌቶ የክትባት ቤተ ሙከራ ውስጥ ሳይንቲስቶች ምርምር እያደረጉ ይገኛሉ። በቤተ ሙከራው ለአምስት ዓመታት የቆየ የሰው ደም ናሙና አለ። ይህም የኢንፍሉዌንዛ ክትባት ላይ ምርምር ሲካሄድ የተገኘ ናሙና ነው። ተመራማሪዎቹ፤ ሰዎች በሌሎች አይነት ኮሮናቫይረሶች መያዛቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ እየፈለጉ ነው። ይህ ማለት ሰውነት ራሱን ከኮቪድ-19 የሚከላከልበት አቅም አዳብሯል ማለት ነው። “ከዚህ ቀደም በሽታን የመከላከል አቅም ማዳበር ተችሎ ሊሆን ይችላል። ቫይረሱ በሌሎች የዓለም ክፍሎች የተስፋፋው ያህል በአፍሪካ ያልተሰራጨውም ለዚህ ይሆናል” ይላሉ ፕ/ር ሻቢር። በተጨናነቀ መንደር የሚኖሩ ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ስለሆኑ ምናልባትም በጊዜ ሂደት ኮቪድ-19ን መከላከል የሚያስችል አቅም አዳብረው ሊሆን እንደሚችል የደቡብ አፍሪካ ሳይንቲስቶች ይገምታሉ። “በከፍተኛ ሁኔታ በተጨናነቁ አካባቢዎች በሽታውን የመከላከል አቅም ሊፈጠር ይችላል። ብዙ ሰዎች ምንም የበሽታው ምልክት የማይታይባቸው ወይም መጠነኛ ምልክት የሚያሳዩት ለዚህ ይሆናል” ሲሉ ፕሮፌሰሩ ያስረዳሉ። የአፍሪካ ድህነት የኮሮናቫይረስ ተጋላጭነትን ቀንሶት ሊሆን እንደሚችልም ያምናሉ። በሌላ በኩል እንደ ብራዚል ባሉ ዜጎች ተጨናንቀው የሚኖሩባቸው አገሮች በርካቶች በቫይረሱ እየተያዙ ነው።
|
https://www.bbc.com/amharic/news-54009884
|
business
|
'ገበሬው አምርቶ የማይጠቀምባት ኢትዮጵያ' የኑሮ ውድነቱን እንዴት መቀነስ ትችላለች?
|
በምጣኔ ሃብታዊ ቋንቋ የአቅርቦት ሰንሰለት ይባላል። በእንግሊዝኛው 'ሰፕላይ ቼይን' የሚባለው ማለት ነው። የአቅርቦት ሰንሰለት ሸማቹ ወይም ተገልጋዩ የሚፈልገው ነገር ለገበያ እስኪቀርብ ድረስ ያለው ሂደት ነው። የምጣኔ ሃብት ሰዎች የአቅርቦት ሰንሰለት የአንዲት ሃገር ዕድገት ምሰሶ ወይም ከምሰሶዎች አንዱ ነው ብንል ማጋነን አይሆንም ይላሉ። የአቅርቦት ሰንሰለትን በቀላል ቋንቋ ለማስረዳት ወደ አርባምንጭ እንሂድ። አርባምንጭ የፍራፍሬ ሃገር ናት። በተለይ ደግሞ ሙዝ። አንድ ፍሬ ሙዝ አርባምንጭ ላይ ያለው ዋጋ እና አዲስ አበባ ተመሳሳይ አይደለም። እንዲሆንም ላይጠበቅ ይችላል። ለምሳሌ አንድ ፍሬ አርባምንጭ ከተማ 20 ሳንቲም ተሸጠ እንበል፤ አዲስ አበባ ሲደርስ ደግሞ 1 ብር [ምሳሌ ነው]። ሙዝ አርባምንጭ በቅሎና አድጎ አዲስ አበባ አሊያም ሌሎች ከተሞች የሚደርሰው የአቅርቦት ሰንሰለትን ተሳፍሮ ነው። አምራች አለ። ከአምራች ተቀብሎ የሚያከፋፍል አለ። ከአከፋፋይ ተቀብሎ የሚቸረችር ይኖራል። ከዚያ ገዥ። ስለ አቅርቦት ሰንሰለት ይህን ካልን ከለት'ተዕለት ኑሯችን ጋር ያለውን ቁርኝት እንይ። አንድ የኢትዮጵያ ኑሮ ሁኔታ የሚያሳስባቸው ግለሰብ፣ አማራ ክልል ውስጥ ያለች አንድ ሽንኩርት አምራች ሥፍራ ያለው የሽንኩርት ዋጋና ከተማ ሲደርስ ያለው ዋጋ እጅግ የተለያየ መሆኑ ያሳስባል ሲሉ በትዊተር ገፃቸው አሥፍረው ነበር። ለመሆኑ የአቅርቦት ሰንሰለትና የኑሮ ውድነት ግንኙነት አላቸው? የአቅርቦት ሰንሰለቱ የተቃና ቢሆን ኖሮ ለውጥ ይመጣል? "እርግጥ ነው ግንኙነት አላቸው። ነገር ግን ሌሎች ምክንያቶች የበለጠ ተፅዕኖ አላቸው" ይላሉ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲው ፕሮፌሰር አለማየሁ ገዳ። "ያለፈውን አሥር ዓመት ብናይ ኢሕአዴግ በገጠርም በከተማም መንገድ ሠርቷል። ግን ከአሥር ዓመት በፊት ያለውን ንረትና አሁን ያለውን ስታየው የዛሬው በጣም ትልቅ ነው። ስለዚህ ሌሎች ገፊ ምክንያቶች ናቸው ለዋጋ ንረቱ ምክንያት የሆኑት እንጂ ሰንሰለቱ ብቻ አይደለም።" ፕሮፌሰር አለማየሁ እነዚህ 'ገፊ' ያሏቸውን ምክንያቶች ያስረዳሉ። ባደረግኩት ጥናት እነዚህ ምክንያቶች አራት ናቸው ይለሉ። "አንደኛው ምርታማነት ነው። ምርታማነታችን በሄክታር ሲሰላ በጣም የሞተ ነው። ለምሳሌ በአማካይ የእርሻ ምርታማነቱ የሚያድገው በዓመት በ2.5 ነው። ይህ ከሕዝብ ቁጥር ጋር ሲነፃፀር ዝቅ ያለ ነው። በእያንዳንዱ የሰብል ዓይነት ሊለያይ ይችላል። ነገር ግን በአጠቃላይ በቂ አይደለም። በጥናቴ መሠረት ቁጥር አንድ ምክንያት ይህ ነው። "ቁጥር ሁለት ያገኘሁት ምክንያት ከ2000 ዓ.ም. ጀምሮ ላለፉት 12/13 ዓመታት ከተገቢው በላይ ብር ይታተም ነበር። ለምሳሌ 2000 ዓ.ም. ላይ የቁጠባ ሒሳብና የቼክ ሒሳብ ውስጥ ያለን ጨምሮ ጠቅላላ ኢትዮጵያ ውስጥ የነበረው ብር 67 ቢሊየን ነበር። አሁን 870 ቢሊየን ደርሷል። ይህ ማለት በአማካይ በ30 በመቶ ያድግ ነበር ማለት ነው ላለፉት 13 ዓመታት።" ፕሮፌሰር ዓለማየሁ የብር መጠኑ ከ4 እና 5 በመቶ መብለጥ አልነበረበትም ሲሉ ይሞግታሉ። ሶስተኛው ምክንያትም ከገንዘብ ጋር የተያያዘ ነው የሚሉት ምሁሩ የኢትዮጵያ ብር አቅም ከዓመት ዓመት እየተዳከመ መምጣቱ ሌላኛው ሰበብ እንደሆነ ይጠቅሳሉ። "በተለይ አዲሱ መንግሥት ከመጣ በኋላ የገንዘባችን አቅም እየወረደ ወይም እየረከሰ መጥቷል። የቀደመው መንግሥት ብዙ ብር ያትም ነበር። አዲሱ መንግሥት ደግሞ ብሩን እያረከሰው ነው። 80 በመቶ የሚሆኑ ከውጭ የምንገዛቸው ነገሮች የኢንዱስትሪ ግብዓቶችና ነዳጅ የመሳሰሉ ናቸው። ስለዚህ ብሩ በረከሰ ቁጥር እነዚህ ዕቃዎች ይወደዳሉ። በ21 ብር የምትገዛው የነበረው አሁን በ40 ብር ነው የምትገዛው ማለት ነው።" ፕሮፌሰር አለማየሁ ወደ አራተኛው ምክንያት ሲመጡ ከላይ ካነሳነው የአቅርቦት ሰንሰለት ጋር የተያያዘ ርዕስ ያነሳሉ። "አራተኛው ምክንያት የነጋዴዎች አለአላግባብ ትርፍ ማጋበስ ነው። ለምሳሌ አንድ ሽንኩርት የሚያመርት ገበሬ የሚያገኘው ገቢና አዲስ አበባ ያንን ሽንኩርት የሚሸጠው ነጋዴ የሚያገኘው ሲነፃፀር ይዘገንናል። ገበሬው ምንም አያገኝም። ባደጉ ሃገራት አንድ ነጋዴ 20 በመቶ ካተረፈ ትልቅ ነገር ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ እኮ መቶ ሁለት መቶ 'ፐርሰንት' ነው የምታተርፈው። መፍትሄውስ? ምሁሩ መፍትሄው ችግሮቹን 'መገልበጥ ነው' ይላሉ። እንዴት ማለት? በዝርዝር ያስረዳሉ። "ለምሳሌ የመጀመሪያው መፍትሄ የሚሆነው ምርታማነትን ማሳደግ ነው። ለምሳሌ ስንዴ ኢትዮጵያ ምን ያክል ታመርታለች? በቆሎስ? ደቡብ አፍሪካ በቆሎ የኛን እጥፍ ነው የምታመርተው። ስለዚህ ምርታማነት ላይ መሥራት ነው አንዱ መፍትሄ።" የምጣኔ ሃብት አስተማሪው ምርታማነት ማሳደግ ትልቅ 'ኢንቨስትመንት' ይጠይቃል ይላሉ። ነገር ግን በአጭር ጊዜ መፍትሄ ለማምጣት ሊደረግ የሚችለው በትናንሽ መስኖዎች ምርት ማምረት ነው ይላሉ። "ጠቅላላ ምርታማነት እንኳ ባይጨምር በዓመት ሁለቴ አመርትን ማለት ነው። ለምሳሌ 5 ኩንታል የምታመርት ከሆነ በዓመት፤ በመስኖ ሁለት ጊዜ አመርትክ ማለት 10 ኩንታል ሆነ ማለት ነው። ስለዚህ የአጭር ጊዜ መፍትሄ ሆኖ የሚታየኝ ይሄ ነው።" ፕሮፌሰር አለማየሁ ካለው የሥራ አጥ ወጣቶች ቁጥር አንፃር ወጣቶች በዚህ መስክ ላይ እንዲሰማሩ ያሻል ይላሉ። እንደ ምሁሩ ከሆነ ሁለተኛው መፍትሄ ጥብቅ የሆነ የገንዘብ ፖሊሲ ማውጣት ነው። ካልሆነ ደግሞ የሚወሰደውን ብድር ከላይ ለተጠቀሰው መፍትሄ ማዋል ይገባል ይላሉ። "የሚታተመው ብር ባለፉት ሶስት ዓመታት እየቀነሰ መጥቷል። ይሄ ቆንጆ እርምጃ ነው። ግን ከዚህ በተጓዳኝ የሚታተመው ብር የት ነው የሚገባው የሚለው ነው። የሚታተመው ብር ምርታማነት ላይ ቢጠፋ ችግር አልነበረውም ነበር። የመጀመሪያውን ችግር በፈታ ነበር።" የምጣኔ ሃብት ባለሙያው ከጠ/ሚ ኃይለማርያም ዘመን ጀምሮ ብር 'ዲቫሉዌት' አልያም አቅሙ መውረድ የለበትም በማለት ሲሞግቱ እንደነበር ይናገራሉ። "ፈረንጆቹ የሚነግሯቸው 'ኤክስፖርት' [የወጪ ንግድ] ይጨምራል፤ 'ኢምፖርትን' [የገቢ ንግድ] ይቀንሳል እያሉ ነው። ባለፉት ሶስት ዓመታት እኛ ማየት አንደቻልነው ኤክስፖርት አልጨመረም፤ ያው ባለፉት አስር ዓመታት በነበረበት [3 ቢሊዮን ዶላር] እንዳለ ነው። ኢምፖርቱ አይቀንስም [ወደ 17 ቢሊዮን ዶላር ነው]። ብርን የማርከስ ጎንዮሽ ጉዳት ከውጭ የሚመጣ ነገር በሙሉ ድሮ በ20 ብር የነበረው አሁን ወደ 40 ከፍ ማለቱ ነው። ይህ ለዋጋ ንረቱ ከፍተኛ አስተዋፅዖ ያደርጋል።" ፕሮፌሰሩ ወደ አራተኛው መፍትሄ ሲመጡ የአቅርቦት ሰንሰለቱ የተስተካከለ ቢሆን ኖሮ የምርት ዋጋ እጅጉን ይቀንስ ነበር ይላሉ። "ያለው አማራጭ መቆጣጠር ነው። ነገር ግን ነጋዴን ተቆጣጥረህ አትዘልቀውም። አዲስ አበባ ውስጥ ብቻ ከ200 ሺህ በላይ ነጋዴዎች አሉ። ይሁንና ልቆጣጠር ብትል ችግር ሊፈጠር ይችላል። "ስለዚህ እኔ የሚታየኝ መፍትሄ ምንድነው፤ በግልና በመንግሥት ትብብር በየቀበሌው ገበያዎችን መመሥረት ነው። በተለይ መሠረታዊ ዕቃዎችን ለሕብረተሰቡ ለማቅረብ። የአምራቾችና የሸማቾች ማሕበር የሚባሉ አሉ። ነገር ግን በሌብነትና በሙስና የተዘፈቁ ናቸው። ስለዚህ የትርፍ ህዳጉን ወስነህ 'ፕሮፌሽናል' የሆነ በግልና በመንግሥት የሚተዳደር [ፐብሊክ ኤንድ ፕራይቬት ፓርትነርሺፕ] ብትመሠርት አንድ መፍትሄ የሚሆን ይመስለኛል።" ምሁሩ እነዚህ ገበያዎች መሠረታዊ ለሆኑ ነገሮች ብቻ ነው መሆን ያለባቸው ይላሉ። "ለዚህ ቆንጆ ምሳሌ 40ና 50 ዓመታት ያገለገሉ ልብ የማንላቸው ተቋማት አሉ። ኢትፍሩትና ከነማ ፋርማሲ የሚባሉ። የእነዚህን ተቋማት 'ስትራክቸር' ማጥናትና በዚያ መሠረት ማቋቋም ይቻላል።" የአቅርቦት ሰንሰለት በኢትዮጵያና በጎረቤት ሃገራት ጎረቤት ሃገር ኬንያ ሁለተኛ ሃገሬ ናት የሚሉት ፕሮፌሰር አለማየሁ የኬንያ መንግሥት ቴክኖሎጂን ተጠቅሞ በገበሬውና በሸማቹ መካከል ያለውን የዋጋ ክፍተት በማጥበብ ትርፉን መልሶ ለገበሬ ማድረግ የሚያስችል ሥርዓት እየዘረጋ እንደሆነ ይናገራሉ። "ዓላማው ትርፉን ወስዶ ለገበሬው ጥቅም ማዋል ነው። ለምሳሌ የጤና ተቋማትን መገንባት፤ ትምህርት ቤት ማሠራት የመሳሰሉትን ለማቋቋም ነው የሚተልመው ይህ ሥርዓት።" ይህን እየቀረፁ ያሉት ኬንያዊ ባለሙያ ልክ እንደ ራይድ ወይም ኡበር ያለን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ሥርዓቱን ተግባራዊ ለማድረግ እየሞከሩ እንዳሉ ፕሮፌሰሩ ያስረዳሉ። "ይህ 'ሲስተም' በኤሌክትሮኒክ አማካይነት ምርቶችንና ሸማቹን ማገናኘት ነው ዓላማው።" ኬንያ ከኛ የሚለያት ቁጥሩ አነስተኛ የሆነና የተደራጀ ነጋዴ መኖሩ ነው ይላሉ ምሁሩ። ስለዚህ ይህ ለቁጥጥር ይመቻል ሲሉ ልዩነቱን ያስረዳሉ። "እኛ አንድ 15-20 ዓመት አይቀረንም ብለህ ነው ኬንያ አሁን ያለችበት ለመድረስ?" የሚሉት ፕሮፌሰር አለማየሁ ኢትዮጵያ መወዳደር ያለባት ከነ ሩዋንዳና ማላዊ ጋር ነው ይላሉ። ምሁሩ ሐሳባቸውን ሲያጠቃልሉ 'ኋላ ቀር መሆናችን ገብቶን ወደ መፍትሄው በፍጥነት ማምራት አለብን' ይላሉ።
|
https://www.bbc.com/amharic/news-56920410
|
politics
|
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን የዘ ኢኮኖሚስት ዘጋቢን ፈቃድ ሰረዘ
|
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን በኢትዮጵያ የዘ ኢኮኖሚስት ጋዜጣ ዘጋቢ የሆነውን ቶም ጋርድነር ፈቃድ መሰረዙን አስታወቀ። ዘጋቢው "የሙያ ስነ ምግባርና የሃገሪቱን ህግና መመሪያ መጣሱንም" በመግለፅ ባለስልጣኑ ለፈቃዱ መሰረዝ ምክንያት እንደሆነ በዛሬው ዕለት ግንቦት 5፣ 2014 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ አስፍሯል። ባለስልጣኑ ጥሰቶች ብሎ ያሰፈራቸውን ጉዳዮች በዝርዝር አልገለጸም። ባለስልጣኑ እዚህ ውሳኔ ላይ ከመደረሱ በፊት ከዚህ ቀደም ከዘጋቢው ቶም ጋርድነር ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶች አድርገናል ብሏል። ባለስልጣኑ ከሳምንታት በፊት ለዘ ኢኮኖሚስት ዘጋቢው ቶም ጋርድነር የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ሰጥቷል። ጋዜጠኛው በግል የማህበራዊ ሚዲያው ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድና የህወሃት መሪ ዶክተር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል ጋር በስልክ ተወያይተዋል የሚል መልዕክት ማስፈሩን ተከትሎ ባለስልጣኑ በሪፖርቱ ላይ በተለይም በብሔራዊ ጥቅም ጉዳዮች ላይ ጥንቃቄ እንዲያደርግ አስጠንቅቋል። ቶም ጋርድነርም ሆነ ዘ ኢኮኖሚስት በዚህ ጉዳይ ላይ እስካሁን ምላሽ አልሰጡም። ነገር ግን ይህ እርምጃ በባለስልጣናቱ የሚዲያ ሽፋንን ለመቆጣጠር የተደረገ ሙከራ ነው በሚል ትችት ቀርቦበታል። በባለፈው አመት ጥቅምት ወር መጨረሻ በትግራይ ጦርነት ከተቀሰቀሰበት ጊዜ ጀምሮ የኢትዮጵያ መንግሥት ለጋዜጠኞች እና ለተቃዋሚዎች አስቸጋሪ ሁኔታን በመፍጠር ይወቀሳል። ከፍተኛ የመብት ጥሰቶች፣ ጅምላ ግድያዎች፣ ደፈራዎች፣ እንደ ጦር ወንጀል ሊቆጠሩ የሚችሉ መጠነ ሰፊ ጥሰቶች ተፈፅመውባቸዋል በሚባሉ የጦርነቱ ስፍራዎች ደርሰን መዘገብ ተከልክለናል በሚልም ጋዜጠኞች ቅሬታቸውን ሲያሰሙ ይሰማል። የጋዜጠኞች መብት ተቆርቋሪው ድርጅት (ሲፒጄ) የጸጥታ ኃይሎች በጦርነት ጊዜ የወጣ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጋዜጠኞችን በዘፈቀደ ለማሰር ተጠቅመዋል ሲል ከቅርብ ወራት በፊት መተቸቱ ይታወሳል። በወቅቱ በእስር ላይ የዋሉ በርካታ ጋዜጠኞች ከእስር ቢለቀቁም ከአገር ውስጥ የሚዲያ ተቋማት ጋር ግንኙነት ያላቸው ሁለት ጋዜጠኞች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ናቸው። ሲፒጄ በተጨማሪም ከሰሃራ በታች ካሉ የአፍሪካ አገራት ጋዜጠኞችን በማሰር ኢትዮጵያ ሁለተኛ ናት በሚል ሪፖርት አውጥቷል። በቅርቡም ድርጅቱ በእስር ላይ ያሉት ደሱ ዱላ እና ቢቂላ አመኑ የተሰኙ ጋዜጠኞች እንዲፈቱና ክሳቸው እንዲቋረጥ ጠይቋል። የማኅበራዊ ሚዲያ የሆነው የኦሮሚያ ኒውስ ኔትወርክ ጋዜጠኞቹ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ጋር በተያያዘ ቢሆንም የታሰሩት፣ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ቢነሳም ደሱ እና ቢቂላ በእስር ቤት እንዳሉና ህገ መንግሥቱን በመፃረር በቀረበባቸው እስከ ሞት የሚያደርስ ከፍተኛ ቅጣት እንደሚጠብቃቸውም ገልጿል። ከ12 ወራት በፊት በተመሳሳይ መልኩ ኢትዮጵያ የኒውዮርክ ታይምስ ዘጋቢን 'ሚዛናዊ ያልሆነ ዘገባ አቅርቧል' በሚል የፕሬስ ፈቃዱን የነጠቀች ሲሆን ይህንን እርምጃም ጋዜጣው 'አምባገነናዊ አካሄድ' እና 'እጅጉን ተስፋ አስቆራጭ' ብሎታል።
|
https://www.bbc.com/amharic/news-61441551
|
politics
|
በአማራ ክልል የፀጥታ ተቋማት ባልደረቦች የነበሩትን ጨምሮ በርካቶች መታሰራቸውን የደኅንነት ምክር ቤት አስታወቀ
|
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነት ምክር ቤት ባወጣው መግለጫ፣ በአማራ ክልል የፀጥታ ተቋማትን “የከዱ” የተባሉ አባሎችን ጨምሮ በተለያዩ ወንጀሎች ላይ ተሳትፈዋል የተባሉ አካላት በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ገለጸ። ምክር ቤቱ ትላንት ሰኔ 1 ቀን 2014 ዓ. ም. ባወጣው መግለጫ ላይ “ከፀጥታ ተቋማት የከዱ አባላትን የመያዝ፣ በተለያዩ ወንጀሎች የተሳተፉ አካላትን በቁጥጥር ሥር የማዋል” ሥራ መከናወኑ ተገልጿል። በአማራ ክልል ባለፉት ሳምንታት መንግሥት “የሕግ ማስከበር” በሚል በወሰደው እርምጃ፣ “ተበትነው የፀጥታ ስጋት ሲሆኑ የቆዩ የጦር መሣሪያዎች የመሰብሰብ፣ በሕገ ወጥ ተግባራት ተሰማርተው የነበሩ አክቲቪስቶችን ሥርዓት የማስያዝ” ሥራ መካሄዱንም የደኅንነት ምክር ቤቱ መግለጫ ይጠቁማል። እነዚህንም “ሕዝቡን ለእፎይታ ያበቁ ተግባሮች” ሲል ምክር ቤቱ ገልጿቸዋል። የፌደራል መንግሥት እና የአማራ ክልል መንግሥት በአማራ ክልል የጦር መሣሪያን በመመዝገብ የጀመሩት ዘመቻ ኋላ ላይ ከ4000 በላይ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር የዋሉበት እንደሆነ ተገልጿል። መንግሥት ዘመቻውን “የሕግ ማስከበር” ቢለውም፣ ዘመቻው መንግሥትን የሚተቹ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎችና ማኅበረሰብ አንቂዎችን እንዲሁም ፋኖ የተባለውን ኢ-መደበኛ አደረጃጀት ኢላማ ያደረገ ነው ብለው የሚከራከሩም አሉ። ምክር ቤቱ የፋኖን ታጣቂዎች በስም ባይጠቅስም ከመንግሥት ፀጥታ መዋቅሮች ውጭ ያሉ የታጠቁ አደረጃጀቶች "እንደፈለጉ" ሊሆኑ እንደማይችሉ በመግለጫው አስፍሯል። “በአገር ውስጥ ኃይልን በብቸኝነት የመጠቀም መብት ለመንግሥት የተሰጠ መብት ነው። ዜጎች በሰላም ጊዜ አልሚ፣ በጦርነት ጊዜ ተፋላሚ መሆናቸውም ከጥንት የነበረ ነው። ያ ማለት አገር ስትወረር ሁሉም ለአገሩ ተፋላሚ ይሆናል። አገር ሰላም ስትሆን ደግሞ ሁሉም ወደ ሕጋዊ ማዕቀፍ ይገባል ማለት ነው” ብሏል። ብሔራዊ የደኅንነት ምክር ቤቱ ሚያዝያ 14 ቀን 2014 ዓ. ም. ስለ አገር አቀፍ የፀጥታና ደኅንነት ያደረገውን ግምገማ ተከትሎ ባስቀመጠው አቅጣጫ፣ ከአማራ ክልል በተጨማሪ በኦሮሚያ እና በቤንሻንጉል ጉሙዝም የተወሰዱ እርምጃዎች እንዳሉ በትናንትናው መግለጫ አትቷል። በመግለጫው መሠረት በኦሮሚያ ክልል “በሺዎች የሚቆጠሩ የሸኔ አባላት ተገድለዋል”። “የሸኔን ልዩ ልዩ ቡድኖች የመደምሰስ፣ ሕገ ወጥ እንቅስቃሴዎችን የማምከን፣ በጠላት እጅ የነበሩ አካባቢዎችን መልሶ የመቆጣጠር፣ መንግሥታዊ መዋቅሩን የማጥራት” እርምጃዎች እንደተወሰዱ ጠቅሶ፣ እነዚህንም “ውጤታማ” ሲል ገልጿቸዋል። ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት የሚለው እና መንግሥት ‘ሸኔ’ የሚለው ታጣቂ ቡድን መካከል ውጊያ ሲካሄድ መሰንበቱ አይዘነጋም። መንግሥት በሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) ታግዞ በተካሄደው በዚህ ውጊያ ንጹሐን ዜጎች ሰለባ መሆናቸውን የኦሮሚያ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በተደጋጋሚ መክሰሳቸው ይታወሳል። በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ “የታጠቁ ሽፍቶችን ሥርዓት ማስያዝና መደምሰስ” መከናወኑን ጠቅሶ እነዚህን ሥራዎች “አበረታች” ሲል ምክር ቤቱ ገልጿቸዋል። በክልሉ ሕገ ወጥ የጦር መሣሪያን የመሰብሰብ እንዲሁም ተፈናቃዮችን ወደ ቀያቸው የመመለሥ ሥራ መሠራቱን አክሏል። በቤንሻንጉል ጉሙዝ በክልሉ መንግሥትና በተለይም የጉሙዝ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጉሕዴን) መካከል ዘላቂ ሰላም ለማውረድ የሚደረጉ ጥረቶች በተደጋጋሚ መሰናክል ሲገጥማቸው ቆይቷል። ከቀናት በፊት በካማሺ ዞን በምትገኘው ምዥጋ ወረዳ በክልሉ ልዩ ኃይሎችና በጉሕዴን ታጣቂዎች መካከል በተካሄደ የተኩስ ልውውጥ ሳቢያ 19 ሰዎች መሞታቸው ይታወሳል። በሌላ በኩል በሶማሌ እና በኦሮሚያ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች “ሊደረግ ታስቦ የነበረው የአል-ሸባብ እንቅስቃሴ በፀጥታ አካላት ቅንጅት ከሽፏል” ሲል ብሔራዊ የደኅንነት ምክር ቤቱ ገልጿል። በደቡብ እና በጋምቤላ ክልሎች “የታጠቁና የተደራጁ ሽፍቶችን መልክ የማስያዝ እንቅስቃሴ” መከናወኑን ጠቅሶ፣ በተጨማሪም የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴን ለመግታትና በተለያዩ ማኅበረሰቦች መካከል የሚከሰቱ ግጭቶችን የመፍታት ሥራ መሠራቱን መግለጫው አትቷል። ምክር ቤቱ “ዓለም አቀፍ የሚዲያ ትኩረትን ለመሳብ የሚፈልጉ” ያላቸው ቡድኖች በአዲስ አበባ በተደጋጋሚ የቃጡትን ጥቃት የፀጥታና ደኅንነት መዋቅሩ ማክሸፉን አያይዞ ገልጿል። መንግሥት በአማራ ክልልና በሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች እየተወሰደ ያለውን እርምጃ በተመለከተ ከዚህ ቀደም ባወጣው መግለጫ፣ የሕግ የበላይነትን ማስከበር የዜጎችን ሰላምና ደኅንነት እንዲሁም የአገርን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ብቸኛው መፍትሄ ነው ማለቱ ይታወሳል። በተለያዩ አካባቢዎች የሚታየውን ሕገ ወጥነትና የሰላም መደፍረስን መንግሥት እንዲቆጣጠር ሕዝቡ በተደጋጋሚ ሲጠይቅ ነበር ያለው መግለጫው፣ ብሔራዊ የፀጥታ ምክር ቤት አስፈላጊው እርምጃ እንዲወሰድ መወሰኑን አስታውሷል። በዚህ መግለጫውም በአጠቃላይ የተጀመረው ሰላምና ጸጥታ የማስፈን እንዲሁም ሕግና ሥርዓትን የማስከበር ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አፅንኦት ሰጥቷል።
|
https://www.bbc.com/amharic/articles/cx87elvg9j7o
|
sports
|
እግር ኳስ ፡ የአውስትራሊያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ማልያ በልካቸው አለመሰፋቱ ቁጣን ቀሰቀሰ
|
የአውስትራሊያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ደጋፊዎች የቡድኑ ማልያ በሴቶች ልክ የለም መባሉን ተከትሎ ቁጣቸውን እያሰሙ ነው። የብሔራዊ ቡድኗ ከሜዳ ውጭ የምትጫወትበት ማልያ በአዲስ መልክ ቢሰራም ለሴቶች የሚሆን የለም ተብለዋል ደጋፊዎች። መቶ በመቶ ከፖሊስተር ጨርቅ የተሠራው አዲሱ ማልያ ባለፈው አርብ ከወንዶቹ ማልያ ጋር ነበር ለገበያ የቀረበው። ነገር ግን የሴቶች ብሔራዊ ቡድኗ በትዊትር ገጿ እንዳስታወቀችው አዲሱ ማልያ በሴቶች ልክ አልተሰራም፤ በወንዶች እንጂ በማለት ያጋጠመውን ችግር ገልጸዋል። 'ማቲልዳስ' በተሰኘ ቅፅል ስም የምትታወቀው ቡድን ይፋ እንዳደረገችው አዲሱ ማልያ እስከ 2022 [በአውሮፓውያኑ] ድረስ በሴቶች ልክ አይሠራም። የአውስትራሊያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን በዓለም ሰባተኛ ናት። የአውስትራሊያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንና ናይኪ የተሰኘው የስፖርት አልባሳት አምራች ያመረቱት አዲሱ ቢጫ ማልያ ገበያ ላይ ፈላጊው በዝቷል። ነገር ግን ማልያው በሴቶች ልክ ባለመሠራቱ ሴቶቹም የሚለብሱት ለወንዶቹ የተሠራውን ነው ተብሏል። ምንም እንኳ የሴቶች ብሔራዊ ቡድን አባላት ማልያውን ለብሰው ፎቶ በመነሳት ማስታወቂያ ቢሰሩም ደጋፊዎች ግን ይህ አላስደሰታቸውም። ብሔራዊ ቡድኗ ችግሩ የሚቀረፈው በአውሮፓውያኑ 2022 አዲስ ማልያ ሲተዋወቅ ነው ብላለች። ደጋፊዎችን ጨምሮ የብሔራዊ ቡድኑ አባላት በሁኔታው የተሰማቸውን ቅሬታ በማኅበራዊ ድር አምባ ገፆቻቸው ላይ ገልፀዋል። አውስትራሊያ 2023 ላይ የሚካሄደውን የሴቶች ዓለም ዋንጫ ታዘጋጃለች። የአገሪቱ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አፈ ቀላጤ ስለጉዳዩ በአንድ ቴሌቪዥን ጣቢያ ተጠይቀው "ተጨማሪ አስተያየት መስጠት አልችልም" ብለዋል። የአውስትራሊያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን 'ማቲልዳስ' አባላት በአውሮፓውያኑ 2019 ከወንዶቹ እኩል ደመወዝ እንዲከፈላቸው መወሰኑ ይታወሳል። በስምምነቱ መሠረት ሁለቱም ብሔራዊ ቡድኖች እኩል ደመወዝና የማስታወቂያ ገቢ ያገኛሉ። አልፎም በአውሮፕላን ሲጓዙ የሚደርግላቸው እንክብካቤና የልምምድ ሜዳ ቁሳቁስ አቅርቦት ከወንዶቹ እኩል እንዲሆን ሆኗል። ነገር ግን አሁንም ወንዶቹ በሚወዳደሩባቸው ውድድሮች ካሸነፉ እንዲሁም ዋንጫ ካገኙ ከሴቶቹ የተሻለ ገንዘብ ያገኛሉ። የወንዶቹ ብሔራዊ ቡድን በዓለም 41ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
|
https://www.bbc.com/amharic/news-54216906
|
Dataset Card for [Dataset Name]
Dataset Summary
MasakhaNEWS is the largest publicly available dataset for news topic classification in 16 languages widely spoken in Africa.
The train/validation/test sets are available for all the 16 languages.
Supported Tasks and Leaderboards
[More Information Needed]
news topic classification: categorize news articles into new topics e.g business, sport sor politics.
Languages
There are 16 languages available :
- Amharic (amh)
- English (eng)
- French (fra)
- Hausa (hau)
- Igbo (ibo)
- Lingala (lin)
- Luganda (lug)
- Oromo (orm)
- Nigerian Pidgin (pcm)
- Rundi (run)
- chShona (sna)
- Somali (som)
- Kiswahili (swą)
- Tigrinya (tir)
- isiXhosa (xho)
- Yorùbá (yor)
Dataset Structure
Data Instances
The examples look like this for Yorùbá:
from datasets import load_dataset
data = load_dataset('masakhane/masakhanews', 'yor')
# Please, specify the language code
# A data point example is below:
{
'label': 0,
'headline': "'The barriers to entry have gone - go for it now'",
'text': "j Lalvani, CEO of Vitabiotics and former Dragons' Den star, shares his business advice for our CEO Secrets series.\nProduced, filmed and edited by Dougal Shaw",
'headline_text': "'The barriers to entry have gone - go for it now' j Lalvani, CEO of Vitabiotics and former Dragons' Den star, shares his business advice for our CEO Secrets series.\nProduced, filmed and edited by Dougal Shaw",
'url': '/news/business-61880859'
}
Data Fields
label: news topic idheadline: news title/headlinetext: news bodyheadline_text: concatenation of headline and news bodyurl: website address
The news topics correspond to this list:
"business", "entertainment", "health", "politics", "religion", "sports", "technology"
Data Splits
For all languages, there are three splits.
The original splits were named train, dev and test and they correspond to the train, validation and test splits.
The splits have the following sizes :
| Language | train | validation | test |
|---|---|---|---|
| Amharic | 1311 | 188 | 376 |
| English | 3309 | 472 | 948 |
| French | 1476 | 211 | 422 |
| Hausa | 2219 | 317 | 637 |
| Igbo | 1356 | 194 | 390 |
| Lingala | 608 | 87 | 175 |
| Luganda | 771 | 110 | 223 |
| Oromo | 1015 | 145 | 292 |
| Nigerian-Pidgin | 1060 | 152 | 305 |
| Rundi | 1117 | 159 | 322 |
| chiShona | 1288 | 185 | 369 |
| Somali | 1021 | 148 | 294 |
| Kiswahili | 1658 | 237 | 476 |
| Tigrinya | 947 | 137 | 272 |
| isiXhosa | 1032 | 147 | 297 |
| Yoruba | 1433 | 206 | 411 |
Dataset Creation
Curation Rationale
The dataset was introduced to introduce new resources to 20 languages that were under-served for natural language processing.
[More Information Needed]
Source Data
The source of the data is from the news domain, details can be found here ****
Initial Data Collection and Normalization
The articles were word-tokenized, information on the exact pre-processing pipeline is unavailable.
Who are the source language producers?
The source language was produced by journalists and writers employed by the news agency and newspaper mentioned above.
Annotations
Annotation process
Details can be found here **
Who are the annotators?
Annotators were recruited from Masakhane
Personal and Sensitive Information
The data is sourced from newspaper source and only contains mentions of public figures or individuals
Considerations for Using the Data
Social Impact of Dataset
[More Information Needed]
Discussion of Biases
[More Information Needed]
Other Known Limitations
Users should keep in mind that the dataset only contains news text, which might limit the applicability of the developed systems to other domains.
Additional Information
Dataset Curators
Licensing Information
The licensing status of the data is CC 4.0 Non-Commercial
Citation Information
Provide the BibTex-formatted reference for the dataset. For example:
@article{Adelani2023MasakhaNEWS,
title={MasakhaNEWS: News Topic Classification for African languages},
author={David Ifeoluwa Adelani and Marek Masiak and Israel Abebe Azime and Jesujoba Oluwadara Alabi and Atnafu Lambebo Tonja and Christine Mwase and Odunayo Ogundepo and Bonaventure F. P. Dossou and Akintunde Oladipo and Doreen Nixdorf and Chris Chinenye Emezue and Sana Sabah al-azzawi and Blessing K. Sibanda and Davis David and Lolwethu Ndolela and Jonathan Mukiibi and Tunde Oluwaseyi Ajayi and Tatiana Moteu Ngoli and Brian Odhiambo and Abraham Toluwase Owodunni and Nnaemeka C. Obiefuna and Shamsuddeen Hassan Muhammad and Saheed Salahudeen Abdullahi and Mesay Gemeda Yigezu and Tajuddeen Gwadabe and Idris Abdulmumin and Mahlet Taye Bame and Oluwabusayo Olufunke Awoyomi and Iyanuoluwa Shode and Tolulope Anu Adelani and Habiba Abdulganiy Kailani and Abdul-Hakeem Omotayo and Adetola Adeeko and Afolabi Abeeb and Anuoluwapo Aremu and Olanrewaju Samuel and Clemencia Siro and Wangari Kimotho and Onyekachi Raphael Ogbu and Chinedu E. Mbonu and Chiamaka I. Chukwuneke and Samuel Fanijo and Jessica Ojo and Oyinkansola F. Awosan and Tadesse Kebede Guge and Sakayo Toadoum Sari and Pamela Nyatsine and Freedmore Sidume and Oreen Yousuf and Mardiyyah Oduwole and Ussen Kimanuka and Kanda Patrick Tshinu and Thina Diko and Siyanda Nxakama and Abdulmejid Tuni Johar and Sinodos Gebre and Muhidin Mohamed and Shafie Abdi Mohamed and Fuad Mire Hassan and Moges Ahmed Mehamed and Evrard Ngabire and and Pontus Stenetorp},
journal={ArXiv},
year={2023},
volume={}
}
Contributions
Thanks to @dadelani for adding this dataset.
- Downloads last month
- 2,369