input
stringlengths 1
130k
⌀ |
---|
ኢትዮጵያ የአዲግራት እስርቤት ግድያና ግጭት የከተማይቱ ነዋሪዎች የሟችና የቁስለኛ ቤተሰቦች እንደሚሉት ግጭቱ የተቀሰቀሰዉ በስፖርት ዉድድር ሰበብ ነዉ።
|
የከተማይቱ ነዋሪዎች የሟችና የቁስለኛ ቤተሰቦች እንደሚሉት ግጭቱ የተቀሰቀሰዉ በስፖርት ዉድድር ሰበብ ነዉ።
|
አረና ትግራይ የተባለዉ ተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ግን በትግራይ ክልል በሚገኙ እስር ቤቶች ዉስጥ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት ይፈፀማል ባይ ናቸዉ።
|
ባለፈዉ ዕሁድ ግጭቱ ከተቀሰቀሰ በኋላ ቢያንስ አስር የአዲግራት ወሕኒ ቤት እስረኞች ወዳልታወቀ ሥፍራ መወሰዳቸዉንም የፓርቲዉ መሪ አስታዉቀዋል።
|
የወሕኒ ቤቱ አዛዦችና የምስራቃዊ ትግራይ የፀጥታ ኃላፊዎች ስለጉዳዩ ለመናገር ፈቃደኛ ዓይደሉም ወይም አልተገኙም።
|
ተመሳሳዩን እርምጃ ለመድገም የሰጠችው ቀነ ገደብ ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀናት ቀርተውታል፡፡
|
ያኔ ወደ ኢትዮጵያ በተመለሱ ኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰውን የስነልቦና እና ማህበራዊ ጉዳት ባለሙያዎች ጥናት አካሄደውበታል፡፡
|
በስነልቦና እና ማህበራዊ ቀውስ እንደተጠቁ ተደርሶበታል ታህሳስ ዓ ም፡፡
|
የዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት ማስተናገጃ ግቢ ውስጥ ከሳዑዲ አረቢያ የተመለሱ ኢትዮጵያውያን ተሰብስበዋል፡፡
|
ከእነርሱ ውስጥ አንዷ የሆነችው ዘይነባ ከሰሜን ኢትዮጵያ ወሎ ወደ ሳዑዲ አረቢያ የተጓዘች ነበረች፡፡
|
ያኔ እምባዋን እያዘራች ለዶይቸ ቨለ እንደዚህ የሚሆን ስላልመሰለኝ ነው፡፡
|
የዘይነባ ድምጽ በሳዑዲ አረቢያም ሆነ በመካከለኛው ምስራቅ በቤት ሰራተኝነት የሚያገለግሉ ኢትዮጵያውያንን ስሜት የሚወክል ይመስላል፡፡
|
ዶ ር አበባው ጥናታቸውን ያከናወኑት የዓለም ጤና ድርጅት ያስቀመጠውን የአእምሮ ደህንነት መለኪያ ተጠቅመው ነው፡፡
|
በጣም የተለያዩ ግፎች ይደራረቡና ይከማቹና መጨረሻ ላይ ጠብቀው የሄዱት ነገር አለ አይደል
|
በገንዘብም የተሻለ ይዞ መምጣት በኑሮም የተሻለ መኖር ቤተሰብን መደገፍ እንዲህ አይነት የጠበቋቸውን ነገሮች አለማግኘት የሚያስከትለው ነገር ጭንቀት ነው፡፡
|
ራስን ዝቅ አድርጎ የማየት ራስን ተጠያቂ አድርጎ የመውሰድ ያልተሳካላት ሰው አድርጎ ራስን የመውሰድ ነገር ይታይባቸዋል ፡፡
|
ለምሳሌ ራሴን አመመኝ ይፈልጠኛል የምግብ ፍላጎቴ ቀነሰ ጨጓራዬን አመመኝ እንደዚህ እንደዚህ የሚሉ መገለጫዎች ውስጥ ይገባሉ፡፡
|
ሌላው በአብዛኛው ከሰዎች ጋር የሚኖራቸው ግንኙነትም የመራቅ ነገር ይሆናል ፡፡
|
ለእነሱ የወጣው ያልተመለሰ ገንዘብ አለ ቤተሰብ ከእነርሱ የሚጠብቀው ብዙ ነገር አለ፡፡
|
የመሸማቀቅ የመሳቀቅ ስሜቶች ሁሉ ከዚህ ውስጥ ሊገቡ ይችላሉ ሲሉ ዶ ር አበባው በጥናታቸው ያስተዋሉትን የስነልቦና ችግር ከእነመንስኤው ያስረዳሉ፡፡
|
የአእምሮ ህምሞችን በሁለት የሚከፍሉት ዶ ር አበባው አሳሳቢው ጠንከር ያለ ቀውስ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡
|
በእዚህ የተጠቁቱ ራሳቸውን የማጥፋት ስሜት በየጊዜው የሚመጣባቸው እንደሆኑ ይገልጻሉ፡፡
|
በጥናቶቻቸው ካስተዋሏቸው ውስጥ በመሀል ለየት ያለ ሀሳብ እየመጣ የሚረብሻቸው ይገኛሉ፡፡
|
ለምሳሌ አንዲቱ ልጅ በቁጥሩ ከሚገለጸው ውጭ በሀተታዊ ጥናት ከገለጸችው ነው የምነግርህ፡፡
|
የቀን ህልም ወይም የቀን ቅዥት የሚሉት ዓይነት ውስጥ ይገባሉ፡፡
|
አንዳንዶቹ እኮ አየር ማረፊያ ላይ ጸጉራቸውን እየነጩ የሚቆሙ አሉ፡፡
|
በተመሳሳይ መልኩ የሳዑዲ ተመላሾች ላይ የደረሰውን ማህበራዊ ጥናት ያጠኑት አቶ ደሳለኝ ቢራራ ስደተኞቹ ማህበራዊ ቀውስ እንደገጠማቸው በጉልህ ማስተዋላቸውን በጥናታቸው አካትተዋል፡፡
|
በዚያን ምክንያት ብዙዎቹ አብሮ ከመኖር ይልቅ እንደገና የመሰደድ ዝንባሌ ነበር የታየባቸው፡፡
|
ሁለተኛው ደግሞ ቤተሰብ የሚጠብቃቸው አምጥተው ያሳልፉልናል ለችግራችን ደራሽ ይሆናሉ ገንዘብ ልከው እኛን ይረዱናል በሚል ነው፡፡
|
እንዲህ አይነትማህበራዊ ችግር የሚገጥማቸው ተመላሾች ሶስት አይነት አማራጮችን አንደሚጠቀሙ አቶ ደሳለኝ በጥናታቸው ጠቁመዋል፡፡
|
አጥኚዎቹ በቀደምት የሳዑዲ ተመላሾች ላይ በታዘቡት ላይ ተመስርተው የስነልቦናም ሆነ ማህበራዊ ቀውስ እንዳይገጥማቸው በቂ ትኩረት ተሰጥቶ አልተሰራም ይላሉ፡፡
|
ተመሳሳይ ችግር በድጋሚ እንዳይከሰት ቅድመ ዝግጅት መደረግ እንዳለበት ይመክራሉ፡፡
|
ስፖርት ስፖርት መጋቢት ቀን ዓ ም ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች ባደረጓቸው ውድድሮች ትናንት ድል ቀንቷቸዋል።
|
ጀርመን ውስጥ በሁለት ከተሞች ማለትም በመዲናዪቱ በርሊን የግማሽ ማራቶን በቦን ደግሞ ኪሎ ሜትር ፉክክር ተደርጓል።
|
ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች ባደረጓቸው ውድድሮች ትናንት ድል ቀንቷቸዋል።
|
ጀርመን ውስጥ በሁለት ከተሞች ማለትም በመዲናዪቱ በርሊን የግማሽ ማራቶን ሲከናወን በቦን ደግሞ የግማሽም የ ኪሎ ሜትርም ውድድር ነበር።
|
የበርሊኑ ወኪላችን ይልማ ኃይለሚካኤል አትሌቶቹን በውድድር ቦታው በመገኘት አነጋግሯቸዋል።
|
ወደዚያ ከማቅናታችን በፊት ግን ቦን ከተማ ውስጥ ወደተደረገው የማራቶን ሩጫ እንሻገር።
|
ትናንት ቦን ከተማ ውስጥ ከ ሺህ በላይ ታዳሚዎች በተገኙበት የማራቶን ሩጫ ሺህ አትሌቶች ተሳታፊ ነበሩ።
|
በውድድሩ ያለፈው ዓመት አሸናፊ ኬኒያዊው ኤድዊን ኮስጌይ አለያም ኢትዮጵያዊው ዘመኑ ወቅርነህ እንደሚያሸንፉ በብዙዎች ዘንድ ተጠብቆ ነበር።
|
ትናንት የቦን ከተማ ከወትሮው ለየት ባለ መልኩ የአየር ጠባዩ አመቺ የሚባል ነበር።
|
ዘመኑ ከኬንያዊው አሸናፊ ደቂቃ ከ ሰከንድ ዘግይቶ ነበር የገባው።
|
በቦን ማራቶን የሴቶች ፉክክር አሸናፊ የኾነችው ኬንያዊቷ ፕሪስካ ኪፕሮኖ ናት።
|
ትናንት ለስለስ ባለው የቦን ከተማ ጸሓያማ ቀን የማራቶን ሩጫ ሲከናወን ነፋሻማ በሆነው በርሊንም የግማሽ ማራቶን ፉክክር ነበር።
|
በበርሊኑ ኛው የግማሽ ማራቶን የሩጫ ውድድር ከ ሃገራት የተውጣጡ አትሌቶች ተሳታፊ ነበሩ።
|
ሺህ የሚቆጠሩ የከተማዋ ነዋሪዎችም ውድድሩንም በተለያዩ አውራጎዳናዎች በመታደም ተከታትለዋል።
|
ኪሎ ሜትር የፈጀው ውድድር ላይ ተሳታፊ የነበሩ አትሌቶችንም አበረታትተዋል።
|
ከበርሊን ግማሽ ማራቶን እና ከቦን የማራቶን ሩጫ ውድድር ባሻገር በሮም ከተማም በዝናማማ የአየር ጠባይ ኢትዮጵያውያን አሸናፊ ኾነዋል።
|
በወንዶች ፉክክር በመሮጥ ኢትዮጵያዊው አትሌት ሹራ ቂታታ አሸናፊ ለመሆን ችሏል።
|
ሲከታተሉት የነበሩት ሁለት ኬንያውያን አትሌቶች ዶሚኒክ ሩቶ እና ቤንጃሚን ቢቶክ ሁለተኛ እና ሦስተኛ ደረጃ አግኝተዋል።
|
በሴቶች ተመሳሳይ ውድድርም አሸናፊ የኾነችው ኢትዮጵያዊቷ ራህማ ጡሳ ስትሆን ውድድሩን ለማጠናቀቅ የፈጀባት ጊዜ ነበር።
|
ኢትዮጵያውያቱ አትሌት መስተዋት ታደሰ እና አበባ ተክሉ ተከትለዋት ሁለተኛ እና ሦስተኛ ወጥተዋል።
|
የኢትዮጵያውያኑ የትናንቱ አመርቂ ውጤት ከግማሽ ምዕተ ዓመት በፊት በከተማዪቱ የነበረውን ድል አስታውሷል።
|
ትናንት በካሊፎርኒያ በተከናወነው የ ሜትር የሩጫ ፉክክር የኦሎምፒክ የብር ሜዳሊያ ባለቤቱ ኢትዮጵያዊው አትሌት ደጀን ገብረመስቀል ለአምስተኛ ጊዜ አሸናፊ ኾኗል።
|
እግር ኳስ በእንግሊዝ ፕሬሚየር ሊግ የእግር ኳስ ግጥሚያ ትናንት አርሰናል ከማንቸስተር ሲቲ ጋር ባደረገው ግጥሚያ ሁለት እኩል በመለያየት ነጥብ ጥሏል።
|
አርሰናል ነጥብ ይዞ ከሚገኝበት ስድስተኛ ደረጃ ወደላይ ፈቅ ለማለት ቀሪ ሁለት ተስተካካይ ጨዋታዎቹን በሰፊ የግብ ልዩነት ማሸነፍ ይጠበቅበታል።
|
ያም ብቻ አይደለም ሁለት ተስተካካይ ጨዋታዎች የቀሩት ማንቸስተር ዩናይትድ እንዲሸነፍም መጸለይ አለበት።
|
ማንቸስተር ዩናይትድ ነገ የሚጋጠመው ሰባተኛ ደረጃ ላይ ከሚገኘው ኤቨርተን ጋር ነው።
|
የፊታችን እሁድ የሚገጥመው ደግሞ ነጥብ ይዞ የደረጃ ሠንጠረዡ ጥግ ኛ ላይ ከሚያጣጥረው ሰንደርላንድ ጋር ነው።
|
በትናንቱ ጨዋታ የደረጃ ሰንጠረዡ ታች የሚገኙት ሚድልስቦሮው እና ስዋንሲ ሲቲም ያለምንም ግብ ተለያይተዋል።
|
የቦን ማራቶን የመጨረሻ መስመር ላይ ታዳሚያን አሸናፊውን ሲጠባበቁ ቅዳሜ ዕለት ኤቨርተንን ለ ያሸነፈው ሊቨርፑል ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
|
መሪው ቸልሲ በክሪስታል ፓላስ ለ በመረታቱ በ ነጥቡ ተወስኗል በሁለተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኘው ቶትንሀም አንድ ተስተካካይ ጨዋታ ይቀረዋል።
|
በጀርመን ቡንደስሊጋ ባየር ሙይኒክ ነጥብ እና የተጣሩ ግቦች ይዞ እየገሰገሰ ነው።
|
ዶርትሙንድ ኛ ደረጃ ላይ ከሚገኘው የሰሜን ጀርመኑ ሐምቡርግ ጋር የሚያደርገው ግጥሚያም ነገ ማታ በተመሳሳይ ሰአት ይከናወናል።
|
ኤኮኖሚ ይነጥፋል የተባለው የስዑዲ ሃብት የሳውዲ አረብያ የተፈጥሮ ሃብት ሃገሪቱን ባለፀጋ እና ተሰሚነት ያላት አገር እንድትሆን አድርጓል ።
|
ይነጥፋል የተባለው የስዑዲ ሃብት በዓለም የገንዘብ ድርጅት ትንበያም የሃገሪቱ የሃብት ክምችት ከጥቂት ዓመታት በኋላ መንጠፍ ይጀምራል።
|
የዛሬዉ ጥያቄ የአያቶላሕ ሩሑላሕ ሆሚኒዋ ታላቅ ሠይጣን የድብቅ ዲፕሎማቶች፥
|
የእስራኤል ኛ ዓመት ምስረታ ቤተ እስራኤላዉያን እስራኤል የተመሰረችበት ኛ ዓመት ነገ በይፋ እንደሚከበር ተገለፀ ።
|
በሺዎች በሚቆጠሩ በእስራኤል ከተሰዉት መካከል በአሸባሪ ጥቃትና በጥበቃ ስራ ላይ ሳሉ በደረሰ አደጋ የተሰዉ ቤተ እስራኤላዉያንም ይገኙበታል።
|
ዛሬ ሲደረግ የዋለዉ የመታሰብያ ሥነ ስርዓት ምሽት ላይ የተሰዉ የእስራኤል ጀግኖችን በሚከብረዉ ችቦ ማብራት ስነስርዓት ይጠቃለላል።
|
በሌላ በኩል ሃገራችንን ወረዋል ሲሉ በሚከሱት ፍልስጤማዉያን ጥያቄ የእስራኤል ሰባኛ ዓመት ምስረታ ጥላ አጥልቶበት ይገኛል።
|
በእስራኤል ስለ ኛ ዓመት ምስረታ ክብረ በዓል በተመለከተ በእስራኤል የቀድሞዉ የአፍሪቃ ስደተኞች ጉዳይ ቢሮ ዋና ተጠሪን አቶ ዮሃንስ ባዩን አነጋግረንናል።
|
አፍሪቃ ሃሚልተን ናኪ፦በአፓርታይድ ወቅት ተመራማሪው ባለሙያ ሃሚልተን ናኪ ከአትክልተኛነት እስከ የጤና ቤተ ሙከራ ረዳትነት የበቁ ሰው ናቸው።
|
የሃሚልተን ናኪ ልደትና ሞት ሃሚልተን ናኪ እጎአ ገደማ ደቡብ አፍሪቃ ውስጥ ሴንቴን በተላለችው መንደር በዛሬው የኬፕ ታውን ምስራቃዊ ክፍል ተወለዱ።
|
የደሀ ቤተሰብ ልጅ በመሆናቸዉ ገና በለጋ ዕድሜያቸው እራሳቸውን ለማስተዳደር ተገድደዋል።
|
ሃሚልተን ናኪ ባለትዳር የአራት ወንዶች እና የአንዲት ሴት ልጅ አባት ነበሩ።
|
እ ጎ አ ግንቦት ቀን ዓ ም በልብ ድካም ህመም ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል።
|
ናኪ በ ዓመታቸዉ የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን እንዳጠናቀቁ ስራ ፍለጋ ወደ ኬፕ ታውን ሄዱ።
|
ናኪ እ ጎ አ በ በቤተ ሙከራ ውስጥ እንስሳትን ይንከባከቡ ነበር።
|
የልብ ሐኪም እና ሳይንቲስት ሮበርት ጎትዝ ናኪ ልዩ ችሎታ እንዳላቸው የተገነዘቡትም በዚህ ወቅት ነው።
|
ኋላም ናኪ የምርምር ሕክምና ትምህርት ቤቱ ውስጥ የቤተ ሙከራ ቴክኒሽያን ሆነው መስራት ጀመሩ።
|
ከጊዜ በኋላ በቤተ ሙከራ ውስጥ በእንስሳት አካላት ላይ ንቅለ ተከላ እንዴት ማከናወን እንደሚቻል ተማሩ።
|
በሰዎች ላይ የመጀመሪያውን የልብ ንቅለ ተከላ ካከናወኑት የልብ ሐኪም ፕሮፌሰር ክሪስቲያን በርናርድ ጋር አብረው መስራት የጀመሩትም በዚህ አጋጣሚ ነው።
|
ናኪ በስራቸው ስኬታማ እየሆኑ የሄዱት ደቡብ አፍሪቃ በአፓርታይድ የዘር መድሎ ሥርዓት በምትገዛበት ወቅት ነው።
|
ጥቁር ስለነበሩም ነጮች ቀዶ ህክምና የሚያካሄዱበት ክፍል እንዲሰሩ አይፈቀድላቸውም ነበር።
|
ጥቁር የጤና ባለሙያ ሠራተኞችም ከነጭ ህሙማን ጋር እንዳይገናኙ በሕግ የተከለከለ ነበር።
|
ስለሆነም የናኪ አስተዋፅዎ ለቀዶ ህክምና የሚያስፈልጉ ቴክኒካዊ ነገሮች ላይ ምርምር በማካሄድ የተወሰነ ነበር።
|
ሃሚልተን ናኪ በመጀመሪያው የልብ ንቅለ ተከላ ወቅት ያበረከቱት አስተዋጽኦ ምን ነበር
|
እ ጎ አ ታህሳስ ቀን በልብ ሐኪም ክሪስትያን በርናርድ በተመራው የቀዶ ህክምና ቡድን ውስጥ ሃሚልተን ናኪ አልተሳተፉም።
|
የነቅሎ ተከላውም የተከናወነው ዴኒዝ ዳርቫል ከተባሉ ሟች ለጋሽ የተወሰደው ልብ ወደ ተቀባዩ ሉዊስ ዋሽካንስኪ በመትከል ነበር።
|
ይኼ ችሎታቸውም በቤተ ሙከራው የቀዶ ህክምና ረዳት ሆነው እንዲያገለግሉ ማዕረግ አሰጥቷቸዋል።
|
ይላል በዚህ ሚናቸዉም ናኪ ለበርናርድ ስኬት መንገዱን ካመቻቸው ቡድን አባል ነበሩ።
|
ሃሚልተን ናኪ በመጀመሪያው የልብ ንቅለ ተከላ የቀዶ ህክምና ወቅት መሳተፋቸውን የተለያዩ ምንጮች ይጠቅሳሉ።
|
የናኪ ታሪክ ግን የብዙ ጥቁር ደቡብ አፍሪካውያንን ታሪኮች የሚያንፀባርቅ ሲሆን ከአመት አመት ደግሞ ጎልቶ እንዲታይ ሆኗል።
|
እ ጎ አ በ የተሰወረ ልብ የሚለው ዘጋቢ ፊልም የናኪ ሚና ዝቅተኛ ግምት ተሰጥቶት ሊሆን እንደሚችል ጠቁሟል።
|
በቅርብ ዓመታትም የናኪ የቤተሰብ አባላት ንቅለ ተከላውን ያደረጉት ናኪ ነበሩ ሲሉ ቁጣቸውን ገልጸዋል።
|
የናኪ ልጅ ቴምቢንኮሲ ናኪ ነገሩ በጣም ነው የጎዳኝ ክሪስትያን በርናንድ ሁሉንም ሽልማት ሲያገኙ አባቴ ግን ምንም አላገኘም ብለዋል።
|
ክሪስታና በርናርድ ስለ ሃሚልተን ናኪ አስተዋጽኦ ምን ይሉ ነበር
|
ክሪስትያን በርናርድ በመጨረሻዎቹ የህይወት ዘመናቸው ለሃሚልተን ናኪ ከፍተኛ ክብር ሲገልፁ ተደምጠዋል።
|
እ ጎ አ በ ናኪ ከኬፕ ታውን ዩኒቨርስቲ የህክምና ሳይንስ የክብር ዲግሪም አግኝተዋል።
|
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.