input
stringlengths 1
130k
⌀ |
---|
በሳዑዲ አረቢያ መገናኛ ብዙሃን ስማቸው ከተዘረዘረ ባለሀብቶች መካከል በኢትዮጵያ በርካታ የንግድ ተቋማት ባለቤት የሆኑት ሼህ መሐመድ ሁሴን አላሙዲ አንዱ ናቸው፡፡
|
መገናኛ ብዙሃኑ ያወጧቸው መረጃዎች ባለሀብቱን ፎቶ ጭምር የያዙ ቢሆንም ከእርሳቸው ወገን የተሰጠ ማስተባበያም ሆነ ማረጋገጫ ባለመሰጠቱ ነገሩን ድፍንፍን አድርጎታል፡፡
|
ጉዳዩን እየተከታተለ የሚገኘው የሪያዱ ዘጋቢያችን ስለሺ ሽብሩ ግን የአላሙዲን መታሰር ከምንጮቼ አረጋግጫለሁ ብሏል፡፡
|
አላሙዲ የተወሰኑት ታሳሪዎች እንዲቆዩ ተደርገውበታል በተባለው የሪያዱ ሪትዝ ካርልቶን ባለአምስት ኮኮብ ሆቴል ውስጥ እንደሚገኙ ምንጮቹ እንደነገሩት ገልጿል፡፡
|
የሞሮኮ መገናኛ ብዙሃን ጥቅማቸው ስለሆነ የእርሳቸውን መታሰር በሰፊው ዘግበውታል ይላል ስለሺ፡፡
|
የሚለውን ለማጣራት በአዲስ አበባ ጉዳዩ ወደሚመለከታቸው ደጋግመን ብንደውልም ምላሽ የሚሰጠን ማግኘት አልቻልንም፡፡
|
የአሁኑ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለመሪነት በዕጩነት በቀረቡ ጊዜ የወረፏቸው ሁሌም በምሳሌነት ይነሳል፡፡
|
ልዑሉ ትራምፕን ለመላው አሜሪካ ማፈሪያ ሲሉ የጠሯቸው ሲሆን ከዕጩነትም ራሳቸውን እንዲያገልሉ ሁሉ ጠይቀዋቸው ነበር፡፡
|
የሪያዱ ስለሺ የልዑል አልወሊድ መታሰር ከባድ እርምጃ ነው ይላል፡፡
|
እርሳቸው ማለት እኮ ታማኝ ሸሪካቸው እና በንጉሳውያን ቤተሰብ ውስጥ የሚታመን አይነት ሰብዕና ያላቸው ሰው ናቸው፡፡
|
በተወሰነ ደረጃም የንጉሳውያን ቤተሰቡን የንግድ ጥቅሞች የሚከታተሉ የነበሩ ናቸው፡፡
|
ለበርካታ የንግድ ሰዎች እርሳቸው ተያዙ ማለት ባጣሙኑ የሚያደናግር ነው ይላሉ የፖለቲካ ተንታኙ፡፡
|
እስከ ቅዳሜ ምሽት ድረስ የሀገሪቱ ብሔራዊ ዘብ ኃላፊ የነበሩት ልዑል ሚጠብ ስልጣናቸውን ተነጥቀው እምብዛም ሳይቆይ ነው ለእስር የተዳረጉት፡፡
|
ልዑል ሙጢብ በአንድ ወቅት አሁን ኛ ዓመታቸውን የያዙትን የንጉስ ሰልማንን ዙፋን የመረከብ ተስፋ የነበራቸው ነበሩ፡፡
|
እንዲያም ሆኖ በሳዑዲ ከፍተኛ ግምት የሚሰጠውን እና የአልሳውድን ስርወ መንግስት የመጠበቅ ኃላፊነት የተሸከመው የብሔራዊ ዘብ ኃላፊነት ይዘው ቆይተዋል፡፡
|
የልዑል ሙጢብ መታሰር የአልጋ ወራሹን የሞሐመድ ቢን ሰልማንን ስልጣን ለማደላደል የተወሰደ እርምጃ አድርገው ከሚያስቡት መካከል የፖለቲካ ተንታኙ ግርሃም ግሪፍትዝ ይገኙበታል፡፡
|
ሞሃመድ ቢን ሰልማን መጀመሪያ የመከላከያ ሚኒስትሩን ቀጥሎ የጸረ ሽብር እና የሀገር ውስጥ ደህንነት አገልግሎትን በእርሳቸው የበላይ ጠባቂነት ስር እንዲሆኑ አደረጉ፡፡
|
የብሔራዊ ዘቡን አመራርን ለመለወጥ የነበሩ ሌሎች ዕቅዶች ቢኖሩም ነገር ግን ቀጥተኛ መነሻ ምክንያቱ ያ ነው ይላሉ ግሪፍትዝ፡፡
|
ይህ የገንዘብ ምዘበራ ጉዳይ በመንግስት ባለስልጣናት ብቻ ሳይሆን ጉዳዩን በቅርበት በሚከታተሉ በተወሰኑ ተንታኞችም ዘንድ የሚቀነቀን እንደሆነ ስለሺ ይናገራል፡፡
|
የሳዑዲ ፖለቲካ ተንታኝ እና ጋዜጠኛ ማንሱር አል አሚር የእስር እርምጃው ከፖለቲካዊ ይልቅ ኢኮኖሚያዊ ምክንያት አለው ብለው ከሚያምኑት አንዱ ነው፡፡
|
በሙስና የተያዙት ሰዎች በከፍተኛ ስልጣን ደረጃ ላይ ያሉና በርካታ ገንዘብም ያላቸው ናቸው፡፡
|
ይህ መሪዎቻችን የኢኮኖሚውን ዘርፍ እንደ ጠቃሚ ጉዳይ መውሰዳቸውን መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው፡፡
|
የፖለቲካ ተንታኙ ግርሃም ግሪፍዝ ግን ጉዳዩ የሙስና ዘመቻ መሆኑ ላይ ጥርጣሬ ያላቸው ይመስላል፡፡
|
እኔ እንደሚመስለኝ ነገሩ በትከክልም የጸረ ሙስና ጉዳይ ቢሆንም መንግስት የሚጠራጠረውን የዓለም አቀፉን ህብረተሰብ ለማሳመን አስቸጋሪ ጊዜ የሚገጥመው ይመስለኛል፡፡
|
ሁሌም ቢሆን ይህ ከፖለቲካ ስሌት እና አጀንዳ ጋር የተያያዘ መሆኑ ላይ ጥርጣሬ ይኖራል፡፡
|
ነገር ግን በዚህ ወቅት ማንም ሰው በሙስና ጉዳይ ሊመረመር እንደሚችል ለብዙዎች በግልጽ መልዕከት ያስቀመጠ ነው ሲሉ የሳዑዲ እስር አንደምታው ያስረዳሉ፡፡
|
ፌስቡክ የአምደመረቦች ሁሉ ቀዳሚ ተጠቃሚዎቹ በቁጥር ወደ ሚሊዮን አሻቅበዋል።
|
የሚሊዮኖችን መረጃ እንደያዘ ሰሞኑን ለአክሲዮን ገበያ መቅረቡ በኒውዮርክ ተጠቃሚዎቹ በቁጥር ወደ ሚሊዮን አሻቅበዋል።
|
በማዕከላዊ ወህኒ ቤት የእስር ጊዜ ኣሳልፌያለሁ የሚሉት አቶ ታዬ ዜናዉን ዉሳኔዉ አስደስቷቸዋል።
|
ዓለም አቀፍ ደረጃዉን የጠበቀ የምርመራ ተቋም ይባል እንጂ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተመሳሳይ የእስረኛ አያያዝ መኖሩን አቶ ተማም ይጠራጠራሉ።
|
በቅርቡ በኦሮሚያ ክልል የፍትህ ቢሮ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች የሥራ ሒደት ኃላፍ ሆነው የተሾሙት አቶ ታዬ በዚህ ላይ የሚጨሩት አለ።
|
ማዕከላዊን መዝጋት አንድ ነገር ሆኖ እያለ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍል መደበኛ ባልሆኑ እስር ቤቶች ዉስጥ ታስረዉ ስለሚገኙት ብዙዎች እጣፋንታም የሚያነሱ አሉ።
|
አቶ ታዬ በፌስቡክ ገጻቸዉ ላይ የጠቅላይ ሚንሥትሩን ንግግር አስመልክተዉ በጻፉት አስተያየት ንግግራቸዉ ህወሀትን ንፁህ አድርጎ ደርግን ብቻ ወንጅሏል።
|
አቶ ኃ ማርያም የህወሀትን ጥፋት በተቻለዉ ሁሉ ለማስተባበል ጥሯል።
|
የሰማያዊ አባላት ፍርድ ቤት ሲለቃቸዉ ፖሊስ ያዛቸዉ አውዲዮውን ያዳምጡ።
|
የኢትዮጵያውያን የትንሳኤ በአል አከባበር በፈረንሳይ ይዘት ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን።
|
ዘ ሄይግ ኔዘርላንድ የሚገኘው ዓለም አቀፉ የጦር ወንጀል ተመልካች ፍርድ ቤት የቀድሞው የኮትዴቩዋር ፕሬዝደንት ሎሮ ባግቦ ላይ የመሠረተውን ክስ አቋረጠ።
|
ሁለቱም ተጠርጣሪዎች ጠበቆች ለቀረበባቸው ክስ በቂ ማስረጃ ባለመገኘቱ ዳኞቹ ክሱን እንዲያነሱላቸው ሲጠይቁ ቆይተዋል።
|
በዛሬው ዕለት ግን አቃቤ ሕግ በቂ ማስረጃ ማቅረብ እንዳልቻለ ያመለከቱት የዓለም አቀፉ ፍርድ ቤት ዳኞች ሁለቱንም ከክሱ ነፃ ብለዋቸዋል።
|
ሎሮ ባግቦ እና ሻርል ብል ጉዴንም በመከላከያው መሠረት ከቀረቡባቸው ክሶች ሁሉ ነፃ በማለትም በአንቀጽ መሠረት ባስቸኳይ እንዲለቀቁም አዝዟል።
|
የዳኞቹ ውሳኔ በፍርድ ቤቱ ውስጥ የተቃውሞ እና ደስታ ጉምጉምታን አስከትሏል።
|
የሁለቱም ተጠርጣሪዎች ጠበቆች ለቀረበባቸው ክስ በቂ ማስረጃ ባለመገኘቱ ዳኞቹ ክሱን እንዲያነሱላቸው ሲጠይቁ ቆይተዋል።
|
ዶይቸ ቬለ ህወሓት ውህደቱን ተቃውሞ ስለመውጣቱ በግንባሩ ውስጥ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት የሆኑ ግለሰቦችን ምልከታ እንዲሁም የኢዜማን አስተያየት አሰባስቧል።
|
በደርግ ጊዜም በአንድ ቀን ስብሰባ ከሌኒን በላይ ሌኒኒዝምን የሰበከ ቄስ በኢትዮጵያ እንደነበር ስታውቅ ደግሞ ነገሩ የተለመደ መሆኑን ትረዳለህ።
|
ያ ማለት ብሔሮችና ብሔረሰቦች ከመቼውም ጊዜ የበለጠ እኩልነትን እና ፍትሃዊነትን በእናት አገራቸው ውስጥ ይጎናጸፋሉ።
|
ያ ማለት አንዳንድ ብሔር ብሔረሰቦች ሁልጊዜ ታሪክ እየተመዘዘ አይደረጉም።
|
ይህ ሁሉ የሚሆነው በውህድ ፓርቲው ውስጥ ነው ሲሉ ጽፈዋል ።
|
የህወሓት የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ አማኑኤል አሰፋ እንዳሉት ህወሓት ከፓርቲም ሆነ መንግሥታዊ ሕግጋት ባፈነገጠ ሂደት ውስጥ መግባት አይፈልግም።
|
እንደዚያ አይነት በኢትዮጵያ ህግም ሆነ በፓርቲው በኢህአዴግም ሆነ ብሄራዊ ፓርቲ የሚመሩባቸው ህጎች እንደዚያ አይልም ብለዋል።
|
አሁን እኔ ስላልተሳተፍኩኝ የስራ አስፈጻሚ አባል ስላልሆንኩኝ ምን እንደነበር ግልጽ የሆነ ዝርዝር ነገሮችን አላገኘሁም ።
|
እኔ በመርህ ደረጃ የህወሓት እና የትግራይ ህዝብ አቋም ግን አውቀዋለሁ።
|
ህወሓት በዚህ በሚካሄደው መንገድ ገብቶ መንቦጫረቅ እንደማይፈልግ ቀድሞ ግልጽ አቋም አውጥቷል ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
|
የሀገሪቱ ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ወደ አንድ አገራዊ ፓርቲ መዋሃዱ በበጎ ጎኑ እንደሚመለከት የገለጸው ደግሞ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ኢዜማ ነው።
|
የፓርቲው ድርጅት ጉዳይ ሊቀመንበር አቶ የሺዋስ አሰፋ እንዳሉት ውህደቱ አገሪቱ ከዘውግ አስተሳሰብ የፖለቲካ ምሕዳር መውጣት ስለመፈለጓ አመላካች ነው።
|
መወዳደር ያለባቸው በዘር በሀይማኖት ወይም በአካባቢ ሳይሆን በሚያመነጩት ሀሳብ ነው ባይ ነኝ።
|
እያንዳንዱን ዜጋም በሰውነት በኢትዮጵያዊነት ማየት አለባቸው የሚል ነው ያለኝ።
|
አጠቃላይ ሃሳቡ ከእኛ ሃሳብ ጋር የሚጣጣም አልነበረም ከዚህ ቀደም።
|
ስለዚህ ወደዚህ መቀየሩ እንደተባለው በፖለቲካ ሜዳው ላይ የሚፈጥረው ልዩነት ይኖራል ሲሉ አቶ የሺዋስ ተናግረዋል።
|
ኢህአዴግ ወደ የኢትዮጵያ ሕዝቦች ብልጽግና ፓርቲ የውህደቱ የመጨረሻ ምዕራፍ የሚያደርሰውን የፓርቲውን ንድፈ ሃሳብ በማጽደቅ ወደ ግንባሩ ጉባኤ ማምራቱን አስታውቋል።
|
በኢሕአዴግ አገዛዝ ደግሞ ከሀገር ተሰደው ሕይወታቸው እስካለፈበት ጊዜ ድረስ ነዋሪነታቸውን በአሜሪካ አድርገው ነበር።
|
ከረዥም ዓመታት የጽሞና ጊዜ በኋላ ላለፉት ሁለት ዓመታት በማኅበራዊ የመገናኛ አውታሮች በተለይም በፌስቡክ ብቅ ብለው በተከታታይ ጽሑፎችን ያቀርቡ ነበር።
|
ባለፈው እሁድ በተወለዱ በ ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ተገልጧል።
|
ስለ አቶ አሰፋ ጫቦ የሕይወት ታሪክ ዶክተር ካሳ ከበደን በማናገር መክብብ ሸዋ ከዋሽንግተን ቀጣዩን ዘገባ ልኮልናል።
|
የሶማሊያ ፕሬዝደንት አላሚ ሶማሊያ ዉስጥ ትወለድ እንጂ በስደት አድጋ ተምራ ነዉ የራሷን ቤተሰብ ያፈራችዉ።
|
አሁን የአራት ልጆች እናት የሆኑት ፋዱሞ ዳይብ በቅርቡ የሶማሊያ የመጀመሪያዋ የሴት ፕሬዝደንት የመሆን ህልም ሰንቀዋል።
|
በጎርጎሪዮሳዊዉ ዓ ም ሶማሊያ ዉስጥ በተባባሰዉ የእርስ በርስ ግጭት ጦርነት ከወላጆቻቸዉ ጋር ታስረዉ ከሀገር ተሰደዱ።
|
የከባድ መኪና ሾፌር ከሆኑ አባት እና ከአርብቶ አደር እናቷ ጋር ኬንያ ዉስጥ የቆዩባቸዉን ጊዜያት ወደኋላ ያስታዉሱታል።
|
የስደት ህይወት ኬንያ ዉስጥ ሳይደላቸዉ የፊንላንድ መንግሥት ጥገኝነት ሰጥቷቸዉ ወደሄልሲንኪ ተጓዙ።
|
በትንሿ የፋዱሞ ዳይብ አዕምሮ ዉስጥ ግን በኬንያም ሆነ ፊንላንድ ማኅበረሰብ ያለመፈለግ ምሬት ተቀርፆ አድጓል።
|
ቀደም ሲል በነርስነት ፊንላንድ ዉስጥ ሲያገለግሉ የቆዩት ዳይብ በተመድ በመቀጠር ወደፑንትላንድ ተጉዛ በሴቶች እና እናቶች የጤና ዘርፍም ሠርተዋል።
|
ለዚህ ያነሳሳቸዉን ሲገልፁ ለፕሬዝድንነት ለመወዳደር ያነሳሳኝ ሶማሊያ ዉስጥ ቀጣይ የደም መፋሰስን የማስቆም የሞራል እና የሲቪል ግዴታ አለብን ብዬ ስለማምን ነዉ።
|
ዳይብ በምርጫዉ ለመፎካከር መዘጋጀታቸዉን በመጪዉ ሐምሌ ወር ለሶማሊያ ምክር ቤት ማቅረብ እና ማረጋገጫ ማግኘት ይኖርባቸዋል።
|
በዚያም ላይ ወደ ሺህ ዶላር ገደማ ማስያዣ ማስገባትም ይጠበቅባቸዋል።
|
በሶማሊያ ማኅበረሰብ ይህ አልተለመደምና ምን ያህል ድጋፍ አገኛለሁ ብለዉ ያስቡ እንደሆነ ከዶቼ ቬለ ለቀረበላቸዉ ጥያቄ ዳይብ እንዲህ ይላሉ።
|
ከዚህ ባሻገር ለአዲሱ ትዉልድ የግለሰቡ ማንነት ሳይሆን የሚያሳስበዉ ወደጠረጴዛዉ ላይ የሚያመጣዉ ምንድነዉ የሚለዉ ነዉ።
|
በዚያም ላይ ከፆታቸዉ ይልቅ ችሎታና እና የአስተዳደር ብቃታቸዉን ነዉ የሚመለከተዉ።
|
ፋዱሞ ዳይብ ይህን ይበሉ እንጂ ከወዲሁ ተከታታይ የግድያ ዛቻዎች ደርሰዋቸዋል።
|
የሶማሊያ የመጀመሪያ ሴት ፕሬዝደንት ለመሆን ያለሙት ዳይብ ይህ በጣም ግራ አጋቢ ነገር ነዉ።
|
በዚያም ላይ እንዲህ ያለ ማስፈራሪ ለሚደርሳቸዉም ሆነ እኔን እንገልሻለን ብለዉ ለሚያስፈራሩኝ ሰዎች ትክክለኛዉን ነገር መሥራት እንዳለብኝም የሚያሳስብ ነዉ።
|
እነዚህ ሰዎች በጣም ስጋት ገብቷቸዋል ማለት ነዉ እኔን በማስፈራራትም ወደሀገሪቱ ላመጣ ያሰብኩት ነገር አስፈላጊ መሆኑን እያመኑም ነዉ።
|
በእኔ ዉስጥ የአስተዳደር ችሎታ ተመልክተዋል ራዕይ ያለዉ መሪ ህዝቡን አገልጋይ መሪ አይተዋል ማለት ነዉ።
|
ምክንያቱም እኔ ኃላፊነቱን ከያዝኩ ህልዊናቸዉ ስጋት ላይ እንደሚወድቅ ያዉቃሉ ማለት ነዉ።
|
ይህ ነዉ ሶማሊያ ዉስጥ በሺዎች ለሚቆጠሩት ሞት ምክንያት የሆነዉ።
|
ቀጣዩ ምርጫ የራሳቸዉን ጥቅም ብቻ የሚያስቡ ጥላቻን የተሞሉ የጎሳ መሪዎች የሚመረጡበት ከሆነ በጣም የተበላሸ ስርዓት ነዉ የሚሆነዉ።
|
በዚህ በአራት ነጥብ አምስት አካሄድ የሚመረጥ ማንኛዉም ፕሬዝደንት ከፍተኛ ብቃት የሌለዉ እና ሙሰኛ ሰዉ ነዉ የሚሆነዉ።
|
በፍቃዱ ኃይሉ ለዶይቸ ቬለ ከምልካቸው መጣጥፎች መካከል የበኩሬ በሆነው እና የኢሕአዴግ ዳግማይ ትንሳዔ ወይስ ዜና እረፍት
|
ይሁንና ከዓመት በኋላ ያንን ድምዳሜዬን የሚያስገመግም ፖለቲካዊ ለውጥ ተከስቷል።
|
አምና ኢሕአዴግ ከጥቂት አባላቱ በቀር በጅምላ ይቅርታ አግኝቶ ነበር አሁን ዓይንህን ላፈር የሚሉት እየበዙ ነው።
|
አምና እምነት ሰጪዎቹ እና ተስፈኞቹ ብዙ ነበሩ ዛሬ ተጠራጣሪዎቹ እና ድንጉጦች በዝተዋል።
|
አምና የግንባሩ አባል ድርጅቶች እየተጎሻሸሙም ቢሆን ኅብረታቸውን እንደጠበቁ ነበር ዘንድሮ ግን አብረን ለመሥራት እንቸገራለን እየተባባሉ ነው።
|
ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ እና አማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ አሁን ዛቻ እና ማስፈራሪያውን ይፋ አወጡት እንጂ በሐሳብ ደረጃ እንደተጣሉ ግልጽ ነበር።
|
እነሆ ተሳክቶላቸው ሥልጣን ከተቆጣጠሩ በኋላ መገለል ደርሶብኛል የሚለውን ሕወሓት አገሪቱ ውስጥ ለተከተለው አለመረጋጋት ተጠያቂ እያደረጉ ከርመዋል።
|
የኢሕአዴግ መፍረስ ምልክቶች ኢሕአዴግ የተመሠረተው በሕወሓት ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም።
|
ይሁንና ሕወሓት በመሠረተው ኢሕአዴግ ውስጥም ይሁን በብዙኀኑ ዘንድ ያልተመጣጠነ የሥልጣን የበላይነት በማከማቸት ሲታማ ኖሯል።
|
በተለይም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከመጡ በኋላ ሕወሓት ኢሕአዴግ ውስጥ ብቸኛ ሀጢያተኛ ተደርጎ መሣሉ የአደባባይ ምሥጢር ነው።
|
ተቃዋሚዎችም ይህንን ሁኔታ የጠላቴ ጠላት በሚል መርሕ ተቀብለው ከቀሪዎቹ የኢሕአዴግ እህት ፓርቲዎች ጋር ስልታዊ ወዳጅነት ጀምረዋል።
|
የኢሕአዴግን መፍረስ የሚያመላክተው ሌላኛው ምልክት የደቡብ ክልል ለመበታተን መዘጋጀቱ ነው።
|
በቅርቡ ከታየው የፖለቲካ ለውጥ ወዲህ በደቡብ ክልል በርካታ ዞኖች የክልልነት ጥያቄ ማንሳታቸው ይታወቃል።
|
እነዚህ አዳዲስ ፓርቲዎች የኢሕአዴግ አባል ሆነው የሚቀጥሉበት ዕድል ያለ ቢሆንም፥
|
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ውሕድ ፓርቲ የመመሥረት ሕልም ሌላኛው የኢሕአዴግ ግንባር መፍረስ አይቀሬ መሆኑን አመላካች ነው።
|
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.