input
stringlengths 1
130k
⌀ |
---|
ይህ ንግግር መቼም ተፈፀመ መቼ የኢሕአዴግ ፍፃሜ አይቀሬ መሆኑን ያመላክታል።
|
በኢሕአዴግ ውስጥ ሥነ ስርዓት መልሶ ማስፈን ለየትኛውም ጠቃሚ ንቅናቄ መፈጠር እንደ ቅድመ ሁኔታ አስፈላጊ ነው።
|
ኢሕአዴግ እንደ ግምባር በጋራ የፈጠረውን ችግር በጋራ ለመፍታት ፈቃደኛ አልሆነም።
|
ይልቁን በግለሰቦች ብሽሽቅ እና ኩራት ምክንያት የብዙኀኑን ጥቅምና ደኅንነት አደጋ ላይ የሚጥል ሌላ አዲስ ገጽታ ያለው ችግር ፈጥሯል።
|
ይህንን ችግር ለመፍታት አባል ድርጅቶቹ በጥሞና የሚያስቡበት ጊዜ አሁን ነው።
|
የዶክተር ነገሪ ሌንጮ ጋዜጣዊ መግለጫ የኢትዮጵያ መንግሥት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስትር በሶስት ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ዛሬ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጡ።
|
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትናንት የመቐለ ኢንዱስትሪ ፓርክን ሲመርቁ እንደተናገሩት ፓርኮቹ በርካታ የሰዉ ኃይል በመቅጠርም የሥራ ዕድሎችን ይፈጥራሉ ብለዋል።
|
የሕገ ወጥ ሰዉ አሸጋጋሪዎችን መረብ ለመከላከል በዓለም አቀፍ የባህር ላይ ያሠማራዉ ተልዕኮ አሉታዊ ዉጤት እንዳለዉ ተቺዎች እየጠቆሙ ነዉ።
|
የአዉሮፓ መርከቦች ከባህር ዳርቻ ሃገራቱ የባህር ክልል ከሆነዉ ከ ማይል ዞን ዉጭ ነዉ የሚንቀሳቀሱት።
|
እዉነት ነዉ ይህ ዘመቻ የመፍትሄዉ አካል እንዲሆኑ ሰዎቹን የመሳብ ሚና አለዉ።
|
እናም የሊቢያ መንግሥታዊ ይዞታ መስመር እስካልያዘ ድረስ ሕገ ወጥ ሰዉ አሸጋጋሪዎቹ ተግባራቸዉን ሊያቆሙ አይችሉም።
|
የሕገ ወጥ ሰዉ አሸጋጋሪዎቹን እንቅስቃሴ ለመግታት የሚደረገዉ የባህሩ ላይ ተልዕኮ አሉታዊ ዉጤት አስከትሏል ከተባለ ይህን ተግባር ማስቆም ታዲያ እንዴት ይቻላል
|
ማርቲን ኮብለር በአንድ በኩል ጠንከር ያለ ርምጃ መዉሰድ ያስፈልጋል።
|
ይህ ወንጀል ነዉ እናም ሰዎቹ ወደ ሕግ ፊት እየቀረቡ መቀጣት አለባቸዉ።
|
በሕገ ወጥ መንገድ አሸጋጋሪዎቹ ሰዎቹን ከሱዳና እና ኒዠር በሰሃራ በረሃ አቋርጠዉ እዚህ ድረስ ያመጧቸዋል።
|
እዚህ ደግሞ በመጠለያ ጣቢያዎች አንዳንዴም መንግሥት በሚያንቀሳቅሰዉ መጠለያ ዉስጥ ይቀመጣሉ።
|
ይህ ደግሞ አንዳንዴ የሰብዓዊ መብቶች የማይከበሩበት ሊሆን ስለሚችል እኛ ስጋት አለን።
|
ማርቲን ኮብለር ላለፉት አንድ ዓመት ሊቢያ ዉስጥ ለተመድ ተልዕኮ ድጋፍ የሚሰጠዉን ተልዕኮ ሲመሩ ቆይተዋል።
|
በዚህ ቆይታቸዉ ግን የታሰበዉን ያህል ማሳካት እንዳልተቻለ ነዉ የጠቆሙት።
|
ማርቲን ኮብለር በተልዕኮዬ ማብቂያ ላይ ያን ያህል ትልቅ የሚባል የሊቢያ መፍትሄ ላይኖር ይችላል።
|
በዚህ ዓመት ባደረግነዉ ደስተኛ አይደለሁም ለምሳሌ ስደትን በተመለከተ ማለት ነዉ።
|
ዓለም አቀፉ ኅብረተሰብ ሊቢያን በተመለከተ ጠንከር ያለ አካሂድ ቢኖረዉ እመኛለሁ።
|
ከዚህ የአዉሮጳ ኅብረት አካል ወደሆነችዉ ወደ ማልታ የ ደቂቃ በረራ ብቻ ነዉ።
|
ሌላዉ ለማርቲን ኮብለር የቀረበዉ ጥያቄ ሊቢያ የከሸፈች መንግሥትና ሀገር ናት ማለት ይቻል ወይ
|
የሚል ነዉ ሊቢያ መንግሥትነቷን ያላረጋገጠች በትክክል አስቸጋሪ ሀገር ናት።
|
ከ ቱ የጋዳፊ አምባገነናዊ ዓመታት በኋላ ሀገሪቱን አንድ አድርጎ ለመምራት በጣም አስቸጋሪ ሆኗል።
|
የሊቢያን ብሔራዊ የጦር ሠራዊት ለማቋቋም የታሰበዉ እንደታቀደ እስካሁን ባይሳካም በቅርቡ ግን ይሳካል የሚል ተስፋቸዉንም ገልጸዋል።
|
ባህል የዓለም ከተማና የፋተርሽቴትን ወዳጅነት ሰላምታና ምስጋናን በአማረኛ ቋንቋ ያቀርባሉ ጀርመናዊዉ የፋተር ሽቴተን ከተማ ነዋሪ።
|
የዓለም ከተማ እና የፋተር ሽቴትን የእህትማማች ማህበት ዋና ተጠሪም ናቸዉ።
|
እስከ ዛሪ ለ ግዜአት ወደ ኢትዮጵያ ሄጄ ሀገሪትዋን ጎብኝቻለሁ።
|
በዚህም ኢትዮጵያን አንድ ቱሪስት ማወቅ ካለበት የበለጠ በደንብ አዉቃታለሁ ማለት እችላለሁ።
|
ገጠር ሄጄ ጎጆ ቤት ዉስጥ ኖሪ አዉቃለሁ በጎጆ ቤት ዉስጥ የሚኖሩ የምረዳቸዉ ቤተሰቦችም አሉኝ።
|
በጎ አ በ ዓ ም ይህ ማህበር ሲቋቋም ማህበሩ ዋና ተጠሪ በመሆን ለአስራ ሰባት ዓመታት አገልግለዋል።
|
በጀርመኗ በፋተርሽታትን ከተማ ነዋሪ የሆኑት የማህበሩ የኮሚቴ አባል ከሆኑ ወ ሮ ራሄል መኮንን ይህን ማህበር ከተቀላቀሉ አምስት ዓመት እንደሆናቸዉ ይናገራሉ።
|
ማህበሩን ተቀላቅለዉ ጀርመናዉያኑ በዓለም ከተማ ለሚገኙ ህዝቦች የሚያደርጉት ስራና ጥረታቸዉን እንዲህ ያደንቃሉ።
|
ማህበራችን በዓለም ከተማና ፋተርሽታትን ከተሞች መካከል ያለዉን ነዋሪ ህዝብ በወንድማማችነት ማስተሳሰር ነዉ።
|
ይህን ስል በመጀመርያ ደረጃ በአካባቢዉ ላይ ለህጻናት ትምህርት ድጋፍ መስጠት ነዉ።
|
እስካሁን ሁለት ህጻናት መዋያ ሰርተናል አንድ አነስተኛ ቤተ መጻህፍትም አለን።
|
በአሁኑ ወቅት ህጻናት በመዋለ ህጻናቱ ለአንደኛ ትምህርት የሚያበቃቸዉን የትምህርት ዝግጅት ያደርጋሉ።
|
በአስተማሪነት እና ህጻናቱን በመጠበቅ ባጠቃላይ አዋቂዎች በዚሁ የማዋለ ህጻናት ተቀጥረዉ ያገለግላሉ።
|
ለህጻናቱ በቂ የማንበብያ ቦታ ስለሌለን ተለቅ ያለ ህንጻ ሰርተን ከሰሞኑ ለማስመረቅ ዝግጅት ላይ ነን።
|
በዚህም የማህበሩ የመጀመርያ ተጠሪ ሴፕ ክሊመንት በጎ አቆጣጠር ዓ ም ኢትዮጵያን ለመጀመርያ ግዜ ለመጎብኘት ይጓዛሉ።
|
ኢትዮጵያ እንደገባሁ የተሰማኝ ይላሉ ሴፕ ክሊመንት በመቀጠል መጀመርያ ወደ ኢትዮጵያ ስሄድ የተሰማኝ ስሜት ከዝያ በፊት የማለዉቀዉ ስሜት ነበር።
|
ልክ ኢትዮጵያ እንደገባሁ ባዕድ ሀገር ሳይሆን እራሴ ሀገር እንደገባሁ ያህል ነበር የተሰማኝ።
|
የሰዉ ልጅ ህይወትን ከ እና በፊት ወደኋላ መለስ ብዪ እንዳይ እንዳስብ አድርጎኛል።
|
በጎ አቆጣጠር ዓ ም ኢትዮጵያ ዉስጥ የገጠመኝ የህዝቡ የአኗኗር ሁኔታ ከ ዓመት በታሪክ የማዉቀዉን የሰዉ ልጅን የአኗኗር ሁኔታ ነዉ።
|
ሰዎች ከባድ ሸክምን እየተሸከሙ በርቀት የሚጓዙበትን ነዉ ያየሁት እናም እነዚህ ሰዎች ለምን ብስክሌትን አልፈጠሩም ስል እራሴን መጠየቄን አስታዉሳለሁ።
|
ግን ሁኔታዉን ጠልቄ ስመለከተዉ እንኳን ስለ ብስክሌት ስለ ተሽከርካሪ ለማሰብ ቀርቶ ለእግር መንገድ አዳጋች ነዉ።
|
በመጀመርያ አካባቢዉ ላይ እንደመጣሁ ሴቶች በእንስራ ዉሃ ተሸክመዉ ረጅም መንገድን ሲጓዙ ነበር ያየሁት።
|
አሁን አሁን ደግሞ በቢጫ ደንበጃን ጭንቅላታቸዉ ላይ ተሸክመዉ ሲሄዱ ተመልክቻለሁ።
|
እና ይህ ሁሉ የባህል የአኗኗር ቀዉስን ሳይሆን በጣም የሚያሳዝን የሚያስጨንቅ ስሜት ነዉ የፈጠረብኝ።
|
የአለም ከተማ እና የፋተር ሽቴትን የእህትማማች ማህበር በዚህ ረገድ ያለዉ የስራ ግልጽነት እስከም ድረስ ነዉ
|
የወቅቱ የባህበሩ ሊቀመንበር ጀርመናዊዉ አንቶን ሽቴፈን እንደሚሉት ከሆነ ማህበራችን በርግጥ እጅግ ግዙፍ የሚባል አይደለም።
|
በዚህም እንደ ትልልቅ ድርጅቶች በታዋቂ የሂሳብ አጣሪዎች ወጪ ገቢ የሚታይበት ሳይሆን የማህበሩ አባላት ወጭ ገቢዉን ይቆጣጠራሉ ዓመታዊ ስብሰባንም ያደርጋሉ።
|
ኢትዮጵያ ደርሰን ስንመጣም ማህበሩ የሰራዉን በቦታዉ ላይ ያለዉን ነገር ለአባላቱ ስብሰባ በመጥራት እናሳዉቃለን።
|
ለሚደርስን ጥያቄዎች በግልጽነት መልስ እንሰጣለን ማህበሩ በኪሱ ያለዉንም ገንዘብ የማህበሩ አባላት ያሳዉቃሉ ገንዘቡን ይቆጣጠራሉ።
|
ይህንኑ ድግስና ጉዞ በቢዲዖ ቀርጸዉ በጀርመን በተለያዩ አጋጣሚዎችም በማሳየት ላይ ናቸዉ።
|
የስደተኞች ሞት ራድዮ ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን።
|
ኑ በኢትዮጵያ ሥሩ የተባለበት መድረክ ራድዮ ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን።
|
ሳምንታዊ በሆነዉ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋዜጣዊ መግለጫ ለሕዳሳዉ ግድብ በሚደረገው የቦንድ ሽያጭ መካከለኛዉ ምሥራቅ ከሚገኙ ዜጎች ከፍተኛው ገቢ መገኘቱም ተነግሯል።
|
መግለጫውን የተከታተለው ዘጋቢያችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ከአዲስ አበባ ዝርዝሩን ልኮልናል።
|
በስድስት ወር ውስጥ ብቻ በ የምርጫ ወረዳዎች መድረስ መቻሉን ገልጿል
|
የፖለቲካው አየር ይበልጥ መዳመን ሲይዝ በብዙ ከተሜ ወጣት ኢትዮጵያውያን ዘንድ የሚጠበቅ አንድ ነገር አለ የኢንተርኔት መቋረጥ፡፡
|
በዚህ ረገድ ባለፈው ሳምንትም ተመሳሳይ ችግር እንዳጋጠማቸው የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች እማኝነታቸውን ሰጥተዋል፡፡
|
ዶይቼ ቬለ ያነጋገራቸው እና ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ አንድ የአዳማ ነዋሪ በተንቀሳቃሽ ስልኮቻቸው ኢንተርኔትን አብዝተው እንደሚጠቀሙ ይናገራሉ፡፡
|
ከዓለም ጋር ከሀገር ውስጥም ከምንም ግንኙነታችን ተቋርጧል ይላሉ የአዳማው ነዋሪ፡፡
|
የከፍተኛ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙት እኚሁ የአዳማ ነዋሪ ለትምህርታቸው የሚጠቅማቸውን መረጃ ብዙውን ጊዜ ከኢንተርኔት ያፈላልጋሉ፡፡
|
ካለፈው ሳምንት ወዲህ ግን ከኢንተርኔት መረጃዎች ማውረድ ዳውንሎድ ይቅርና ከጓደኞቻቸው ጋር እንኳ መልዕክት መለዋወጥ አልቻልኩም ይላሉ፡፡
|
የግድ ሲሆንባቸው ግን ብሮድባንድ እና ገመድ አልባ የኢንተርኔት ግንኙነት ያለባቸው ቢሮዎች እየሄዱ ደጅ ይጠናሉ፡፡
|
የተንቀሳቃሽ ስልክ ኢንተርኔት አገልግሎት ወደነበረበት ይመለሳል በሚል በየጊዜው መሞከራቸውንም አልተውም፡፡
|
እኛ ለዛሬ ማታ ዳውንሎድ እናደርጋለን ብለን ከገዛን ወይም ዛሬ ቀን ካደረግን ከ ሰዓት በኋላ የለም፡፡
|
የአዳማው ነዋሪ የኢንተርኔት መቋረጡ በእርሳቸው ከተማ ብቻ ሳይሆን በሌሎች የኦሮሚያ አካባቢዎችም እንደሚስተዋል ይናገራሉ፡፡
|
የአዳማውን ነዋሪ እማኝነት ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ የሱሉልታ ነዋሪም ይጋራሉ፡፡
|
በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች የኢንተርኔት ብቻ ሳይሆን የመደበኛ የተንቀሳቃሽ አገልግሎት የኔትወርክ ችግር እንዳለ ከዘመድ ጓደኞቻቸው መስማታቸውን ይናገራሉ፡፡
|
የኔትወርክ ሙሉ ለሙሉ የመቋረጥ ችግር ትላንት ማክሰኞ ታኅሳስ በሱሉልታም ተከስቶ እንደነበር ያስረዳሉ፡፡
|
በአካባቢያቸው ስላለው የተንቃሳቃሽ ስልክ የኢንተርኔት አገልግሎት ችግር ደግሞ ተከታዩን ብለዋል፡፡
|
በተለይ በኦሮሚያ ክልል ወደዚህ ወደ ሱልልታ ጭራሽ ዳታው አይከፍትም፡፡
|
የሱሉልታው ነዋሪ የኢንተርኔት አገልግሎት መስተጓጉሉን ከባድ ችግር ነው ይሉታል፡፡
|
በሀገሪቱን ሁኔታ አንዳንድ የምናገኘውን መረጃ አለማግኘት ራሱ በጣም ከባድ ነው ይላሉ ነዋሪው፡፡
|
ከሱሉልታ አቅራቢያ በምትገኘው በመዲናይቱ አዲስ አበባም የኢንተርኔት ችግር ይስተዋላል፡፡
|
አገልግሎቱን በተለይ ማግኘት የማይቻለው የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎችን ለመጠቀም ሲሞከር እንደሆነ ተገልጋዮች ይናገራሉ፡፡
|
ማንነቱ እንዳይገለጽ የሚፈልግ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ባለሙያ ይህን የተጠቃሚዎችን አስተያየት ያረጋግጣል፡፡
|
በተለይ ደግሞ ቫይበር እና ዋትስ አፕ ላይ የጽሁፍ ግንኙነት የተፈቀደ ቢሆንም ፎቶዎች እና ቪዲዮዎችን መለዋወጥ የተከለከለ ነው፡፡
|
ምክንያቱም ለምሳሌ ጠዋት አካባቢ ቫይበርም ሆነ ዋትስ አፕ አይሰራም ነበር፡፡
|
ግልጽ ሆኖ እነኚህ ተዘግተዋል እነዚያ አይዘጉም ለማለት የሚያስቸገርበት ቦታ ላይ ነው ያለነው ይላል ባለሙያው፡፡
|
በኢትዮጵያ ያሉ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች እንዲህ እንዳሁኑ ጊዜ በማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎችን እንዳይጠቀሙ እቀባ ሲጣልባቸው እገዳውን ጥሰው አገልግሎቱን የሚያገኙባቸው ዘዴዎች ነበሩ፡፡
|
እንደ ሳይፎን ኦፔራ ማክስ እና አልትራሰርፍ አይነት አፕልኬሽኖችን በመጠቀም የተከለከሏቸውን ድረ ገጾች ሲጎበኙ ቆይተዋል፡፡
|
ባለፈው ሳምንት መጀመሪያ የነበረው የኢንተርኔት እገዳ እነዚህንም ከአገልግሎት ውጭ ያደረገ ነበር፡፡
|
ከቀናት በኋላ የተወሰኑት እንደቀድሞው መልሰው አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን ተጠቃሚዎችም ሆነ ባለሙያው ይገልጻሉ፡፡
|
በኢትዮጵያ እንዲህ ሄድ መለስ የሚል የኢንተርኔት አገልግሎት ማግኘት ለተጠቃሚዎች እንግዳ ነገር አይደለም፡፡
|
ኢንተርኔት ተዘጋ ሲባል ግን ወይ ሙሉ ለሙሉ አገልግሎቱ ይቋረጣል አሊያም የተወሰኑ አገልግሎቶች ተለይተው እገዳ ይጣልባቸው ነበር፡፡
|
የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ባለሙያው ባለፈው ዓመት ከግንቦት ወር መጨረሻ ግድም ጀምሮ የነበረውን የኢንተርኔት መቋረጥ ከአሁኑ የአገልግሎቱ እቀባ ጋር ያነጻጽራል፡፡
|
ባለፈው ዓመት መጀመሪያ አካባቢ የሆኑ ድረገጾች ወይም የሆኑ አፕልኬሽኖች በግልጽ ተዘግተው ነበር፡፡
|
ጭራሽ የሆነ ጊዜ ላይ ምንም አይነት የ ግንኙነት በስልክም በኮምፒውትርም በኤድኤስኤልም በገመድ አልባም የለም ነበር፡፡
|
ከዚያ በኋላ ወደ ተመጣና የቀሩት ድረ ገጾች ተለቀቁ ማለት ነው፡፡
|
ስለዚህ ነገ ደግሞ ያለው ሁኔታ አሁን የሆነ ነገር ብልህ ተቀይሮ ነው የሚጠብቅህ ሲል በየጊዜው ተለዋዋጭ ስለሆነው የኢንተርኔት አዘጋግ ያስረዳል፡፡
|
እንዲህ በየጊዜው ተቀያያሪ በሆነው የኢትዮጵያ የኢንተርኔት ክልከላ ለተጠቃሚዎች ሁነኛ መላ የሆነው የ ግንኙነትን አሊያም ፕሮክሲ ሰርቨሮችን መጠቀም ነው፡፡
|
ኢንተርኔት በሚዘጋባቸው በሌሎች ሃገራትም በመፍትሄነት እያገለገሉ ስለሚገኙት ስለእነዚህ ሁለት ዘዴዎች ባለሙያው ማብራሪያ አለው፡፡
|
በኢንተርኔት ውስጥ የትም አካባቢ ሆነህ የራስህ የሆነ ትንሽዬ ኔትወርክ መፍጠር ነው ፡፡
|
በመላው ዓለም ባሉ የተወሰኑ ኮምፒውተሮች ላይ እንደዚያ አይነት ኔትወርክ መስራት ነው የ ሀሳብ፡፡
|
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.