input
stringlengths 1
130k
⌀ |
---|
ኒክሰን የማኦዋን ቻይና መጎብኘታቸዉን በዩናይትድ ስቴትስ የሚደገፉት የታይፔ የቶኪዮና የሶል መሪዎች አጥብቀዉ ተቃዉመዉት ነበር።
|
ጉብኝቱ የዩናይትድ ስቴትስ ፖለቲከኞችን የፖለቲካ አዋቂዎችን ጋዜጠኞችንና ያኔ ብዙም የማይታወቁትን የመብት ተሟጋቾችንም በመደገፍና በመቃወም ለሁለት የገመሠ ነበር።
|
በ ኛ ዓመቱ ዘንድሮ ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ በኢትዮጵያ ሊያደርጉት ያቀዱት ጉብኝት በዓላማ በይዘት በክብደት ቅለትም ከኒክሰን ጋር በጭራሽ የሚስተካከል አይደለም።
|
ሁለቱ ጉብኝቶች በአላማ ይዘት ክብደት የመለያየታቸዉን ያክል አንድ የሚሆኑበት አንድ ምክንያት መኖሩ ሐቅ ነዉ።
|
ዘመን የማይሽረዉ ዓለም የሚያዉቀዉ እነሱም የሕዝብና የሐገር ብሔራዊ ጥቅም እያሉ የሚያንቆለጳጵሱት ዕዉነት።
|
እርግጥ ነዉ ኦባማ በያዝነዉ ወር ያደርጉታል የተባለዉ ጉብኝት አሜሪካኖችን ሊያከራክር ቀርቶ መሪዉ ጥንታዊቱን አፍሪቃዊት ሐገር እንደሚጎበኙ የሚያዉቀዉም ጥቂት ነዉ።
|
የሚያዉቁትም ያላወቁት ቢያዉቁትም የጉብኝቱ ዓላማ በትልቅቱ ሐገር የመርሕ መዘዉር ላይ የሚሾር መሆኑን እንደሚያዉቁት ለማወቅ ተንታኝ አያስፈልግም።
|
የታቀደዉ ጉብኝት ወትሮም አንድ ያልሆኑትን ኢትዮጵያዉያንን ግን እሁለት ገምሶ ለማነታረክ ለአደባባይ የተቃዉሞ ሰልፍ ለማሳደምም ትልቅ ርዕስ ነዉ።
|
ተወዛጋቢዎች ለየአቋማቸዉ ማስረገጪያ የሚያቀርቧቸዉ ምክንያቶች የመቃረናቸዉን ያክል የጉብኝቱ ዋና መሠረት አንድ መሆኑን እኩል ያዉቁታል።
|
ተከሳሾቹ አሉ እንደተባለዉ ፍርድ ቤቱን እንደ ፍትሕ ማዕከል ሳይሆን እንደ የመንግሥት ባለሥልጣናት ትዕዛዝ ፈፃሚ መቁጠራቸዉን አለመሸሻጋቸዉ እንጂ ክፋቱ።
|
ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹ እንዳሉት ሆነም አልሆነ ተከሳሾች በአስር ቀን ዉስጥ የቅጣት ማቅለያ እንዲያቀርቡም ወስኗል።
|
በልማዱ የቅጣት ማቅለያዉን የሚያቀርቡት ወይም የሚያዘጋጁት የተከሳሾች ጠበቆች ናቸዉ።
|
የፍትሕ ሚንስቴር ባለሥልጣናትን መልስ እንዲሰጡ በተደጋጋሚ ሥልክ ብንደዉልም ልናገኛቸዉ አልቻልም።
|
በዚሕም ምክንያት መታሰር መከሰሷ እንጂ የታሰረችበት ትክክለኛ ምክንያት አይታወቅም።
|
እንደ እስራቱ ሁሉ መለቀቋ እንጂ የተለቀቀችበት ትክክለኛ ምክንያት አይታወቅም።
|
ከዓመት ከሰወስት ወር በፊት ከዘጠኝ ባልረቦቹ ጋር ድንገት ታሰረ።
|
ከአሸባሪዎች ጋር በመተባበር ወንጀል ተከስሶ የፍርድ ቤት ቀጠሮ ሲጠብቅ ድንገት ክሱ ተሰርዟል አንተም ተለቀሐል አሉት።
|
የፌስ ቡክ ምፀተኞች ደግሞ ብዙ እስረኞች እንዲፈቱ ምናለ ኦባማ ኢትዮጵያን ደጋግመዉ ቢጎበኙ።
|
ለመብት ተማጋቹ ለያሬድ ሐይለማርም ግን ድንገት የመፍታቱ ዘመቻ ጥቅም የተሰላበት ግን የዘፈቀደ ፖለቲካዊ ዉሳኔ።
|
ኢትዮጵያ የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ጥረት በትራፊክ አደጋ በርካታ ሰዎች ከሚሞቱባቸው ሃገራት አንዷ ኢትዮጵያ ናት።
|
በኢትዮጵያ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ችግሩን ለመቀነስ ይረዳሉ ያሏቸውን ልዩ ልዩ ጥረቶች እያደረጉ ነው።
|
ከመካከላቸው በብሉምበርግ በጎ አድራጎት ድርጅት አስተባባሪነት በኢትዮጵያ የመንገድ ደህንነትን በማሻሻል ጤናማ ከተሞችን ለመገንባት የሚከናወነው ሥራ አንዱ ነው።
|
የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ጥረት ለሰዎች ሞት እና የጤና ችግሮች ምክንያት ከሆኑት መካከል የመኪና አደጋዎች ተጠቃሽ ናቸው።
|
በየዓመቱ በትራፊክ አደጋ በርካታ ሰዎች ከሚሞቱባቸው ሃገራት አንዷ እና ግንባር ቀደምዋ ኢትዮጵያ ናት።
|
አደጋው አሳሳቢ በሆነባት በኢትዮጵያ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ችግሩን ለመቀነስ ይረዳሉ ያሏቸውን ልዩ ልዩ ጥረቶችን እያደረጉ ነው።
|
ሰሞኑን ከተለያዩ የአፍሪቃ ሃገራት የመጡ ባለሞያዎች በተለይ በአዲስ አበባ ችግሩን ለመከላከል የተከናወኑ ሥራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
|
ጉብኝቱን የተከታተለው የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ዝርዝር ዘገባ አዘጋጅቷል።
|
የማሻሻያ መርሐ ግብሩ ቢሊዮን ብር ገደማ ቢሊዮን ዶላር ይፈጃል
|
ዓለም የሳኻሮብ ሽልማት በዐረቡ ዓለም አምና ስለተቀሰቀሰው የዴሞክራሲ ጥያቄና የለውጥ ትግል በየጊዜው እስካሁን ብዙ በመጻፍ ላይ ነው።
|
የህዝብ ሰፊ አመጽ ረጅም ጊዜ በሥልጣን ላይ የቆዩ አምባገነን መሪዎች እንዲገረሰሱ አድርጓል።
|
ለውጥ ካስገኘው ከህዝባዊው ንቅናቄ በስተጀርባ አንዳንድ ለውጥ እንዲቀሰቀስ ያደረጉ አንዳንድ ግለሰቦች መወሳታቸው አልቀረም።
|
ከእነዚህም መካከል ቱ በዛሬው ዕለት እሽትራስቡርኽ ውስጥ በአውሮፓ ፓርላማ የሳኻሮቭ ሽልማት ተሰጥቶአቸዋል።
|
በዚህ ርእሰ ጉዳይ ላይ እሽቴፋኒ ዱክሽታይን ያቀረበችውን ዘገባ ተክሌ የኋላ እንደሚከተለው አጠናቅሮታል።
|
የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዚዳንት የርዚ ቡዜክ ባለፈው ጥቅምት የዘንድሮዎቹን የሳኻሮቭ ሽልማት አሸናፊዎች ሲያስታውቁ ልዩ ስሜት እንዳሳደረባቸው በድምጻቸው ይታወቅ ነበር።
|
የአውሮፓ ፓርላማ የዘንድሮውን ለመንፈስ ነጻነት የሳኻሮብን ሽልማት ለ የዐረቡ ዓለም የጸደይ ወቅት ተወካዮች ያቀርባል።
|
ቱኒሲያዊው የፍራፍሬና አትክልት ነጋዴ ሞሐመድ ቡዓዚዚ ገና የ ዓመት ወጣት ነበረ።
|
ድምፅ የተቃውሞ በ ኛው ሳምንትም ሞሀመድ ቡዓዚዚ ሀኪም ቤት ውስጥ ህይወቱ አለፈች።
|
ይሁን እንጂ ራሱን አቃጥሎ ህይወቱን ማሳለፉ በመላይቱ ቱኒሲያ የተቃውሞ ማዕበል ቀሰቀሰ።
|
በቱኒሲያ ብቻ ሳይሆን የተቃውሞው ማዕበል ወደ ሌሎቹ የዐረብ ሃገራት ተሸጋገረ።
|
የቀረጸችውን የቪዲዮ ፊልም በ ፌስቡክ ዓምድዋ ላይ እንዲታይ ለቀቀችው።
|
ወደ ታህሪር አደባባይ ብቅ በሉና እጅ ለእጅ ተያይዘን እንነሣ
|
ልባዊ የሆነውን የነጻነት ጥሪዋን የተገነዘቡ በመቶ ሺ የሚቆጠሩ ግብጻውያን ተቀበሉላት።
|
ማኅበራዊ ፍትኅ መሠረታዊ መብት የዴሞካራሲ ተኃድሶ ለውጥ ያቀረበቻቸው ጥያቄዎች ነበሩ።
|
በአሁኑ ጊዜ አስማ ማኅፉዝ ገደማ የፌስቡክ ደንበኞች ወይም ወዳጆች አሏት።
|
ግብጻዊቷ አስማ ማህፉዝ ዛሬ ሽልማት ስትቀበል ባሰማችው ንግግር እንዲህ ነበር ያለች።
|
በዚህ አገር የምኖርና ከአነርሱ መካከል አንዷ በመሆኔ ኩራት ይሰማኛል።
|
የጀርመን ፕሬዝዳንት ፍራንክ ሻልተር ሽታይንማየር በጋና ያካሄዱትን የሁለት ቀናት ጉብኝት አጠናቀው ዛሬ ጋምቢያ ገብተዋል።
|
የአምነስቲ መግለጫ ራድዮ ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን።
|
የጤፍ የባለቤትነት መብትን የማስመለስ ዘመቻ ይዘት ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን።
|
አሁን በለውጥ ሂደት ላይ በምትገኘው በኢትዮጵያ ባለፉት ወራት የሰብዓዊ መብት ይዞታ የመሻሻል አዝማሚያ እያሳየ ነው የሚሉ አስተያየቶች ይሰጣሉ።
|
በሰው ልጅ መገኛነትና በተለያዩ ቅርሶችዋ የምትታወቀው ጥንታዊቷ ሀገር ኢትዮጵያ እንደ እድሜዋ የሚያኮራ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ታሪክ የላትም።
|
ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በየዓመቱ በሚያወጧቸው ዘገባዎች በሀገሪቱ ይፈጸማሉ የሚባሉ የመብት ጥሰቶችን በዝርዝር ሲያሳውቁ ቆይተዋል።
|
የዛሬው እንወያይ በለውጡ ሂደት በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ይዞታ ላይ ያተኩራል።
|
የሕዋ ቴክኒዎሎጂ ብሔራዊ ፖሊሲ በኢትዮጵያ ኢትዮጵያ በ ዓም ጥቅምት ወር ላይ ሳተላይት እንደምታመጥቅ የኢትዮጵያ ሕዋ ሳይንስ ቴክኖሎጂ ተቋም አስታወቀ።
|
ሊዲያ በፈረንሳይ የሚካሔደውን የዓለም ዋንጫ ለመዳኘት ከተመረጡ ሦስት አፍሪቃውያን መካከል አንዷ ናት።
|
ኢትዮጵያዊቷ የእግር ኳስ ጨዋታ ዳኛ ሊዲያ ታፈሰ ከስድስት ወር በኋላ ለሚካሔደው ለስምንተኛው የዓለም የሴቶች ዋንጫ ዝግጁ መሆኗን ለ ተናግራለች።
|
ኢትዮጵያውያኑ ጋዲሳ ሹሜ እና ባለው ደረሰ ሁለተኛ እና ሦስተኛ ሆነው አጠናቀዋል።
|
በዕለቱ የስፖርት መሰናዶ ከእነዚህ ርዕሰ ጉዳዮች በተጨማሪ በሳምንቱ መገባደጃ የተካሔዱ የተለያዩ ጨዋታዎችን ይዳስሳል።
|
ባለፈው ሰኞ ህዳር ቀን በቤልጄየም መዲና ብራስልስ የተሰባሰቡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች የልማት ስብሰባ አካሂደው ነበር።
|
በአማራ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች የሀሰተኛ ምስክር በዜጎች ላይ ተፅዕኖ እየፈጠረ እንደሆነ ነው የፍትህ አካላትና ነዋሪዎቹ የሚገልፁት፡፡
|
ችግሩ በክልሉ ምክር ቤት ጉባዔዎች ሳይቀር በተደጋጋሚ እየቀረበ ውይይት ቢደረግበትም መሻሻል እንዳልታየበት ነው የአነጋገርናቸው አካላት የሚናገሩት፡፡
|
የችግሩ የስፋት መጠን ሰፊ መሆኑን የሚናገሩት አቶ አማረ ይህን ለማወቅ ጥናት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡
|
የደ ሱዳን የረሃብ አደጋና ስጋቱ በርስ በርስ ጦርነት በተመሰቃቀለችዉ ደቡብ ሱዳን ዉስጥ በሚሊዮኖች የሚገመቱ ዜጎች ለምግብ እጥረት መጋለጣቸዉ ተገለጸ።
|
የተመድ የዝናቡ ወቅት እየቀረበ በመጣበት በዚህ ወቅት ለእርሻ መዘጋጀት በማይታሰበብት ሁኔታ የገጠመዉ የምግብ እጥረት የከፋ ቀዉስ እንዳያስከትል አስጠንቅቋል።
|
ከታህሳስ ወር አንስቶም ከ በላይ ሰዎች ከቤት ንብረታቸዉ ተፈናቅለዋ።
|
በተለያዩ አካባቢዎች ለሠፈሩ ወገኖች የምግብ ርዳታ ለማድረስም ዉጊያዉ እንቅፋት እንደሆነበትም ድርጅቱ ሲያመለክት ቆይቷል።
|
እናም ከዚህ ቀደም የምግብ እጥረት የመኖሩ እዉነታን በማሰብ በግጭቱ ምክንያት በርካቶች ከቤት ንብረታቸዉ ስለተፈናቀሉ ችግሩ የከፋ ሊሆን እንደሚችል በመገመት ነዉ።
|
በአሁኑ ጊዜም በብዛት ከዩጋንዳ ይመጣ የነበረዉ የምግብ አቅርቦትም የንግድ እንቅስቃሴዉ በመስተጓጎሎ ሙሉ በሙሉ ተቋርጧል።
|
አንድሩዉ አታ አሳሞሃ ችግሩ ሳይባባስ አሁን ባለበት ደረጃ የሚሰነዘረዉ ማሳሰቢያ አዎንታዊ ነዉ ይላሉ።
|
ዓለም ዓቀፉ ኅብረተሰብ ሊያደርገዉ የሚችለዉን አስመልክተዉ ደግሞ የማምረቱ ሂደት በተስተጓጎለበት በዚህ ወቅት ሊያደርጉ የሚችሉት የእርዳታ ጥሪ ማስተላለፍና አስቀድሞ ማቀድ ነዉ።
|
የተመድ ተቋማትም ደቡብ ሱዳን ዉስጥ ርዳታዉን ለማዳረስ ግፊት ያደርጋሉ።
|
እናም በዚህ ተግባር የሚሳተፉት ሁሉ ዝግጅት እንዲያደርጉ በበቂ ሁኔታ አስቀድሞ የተሰጠ ማስጠንቀቂያ ነዉ ብዬ አስባለሁ።
|
በዚህም ዓለም ዓቀፉ ኅብረተብ በመንግስታቱ ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ፅህፈት ቤት የሚታየዉን ችግር ለመቅረፍ አቅም እንዲኖረዉ ድጋፋቸዉን ሊሰጡ እንደሚገባም አመልክተዋል።
|
ለችግሩ መፈጠርና መባባስ ምክንያት የሆነዉ የቀጠለዉ የፖለቲካ ተቀናቃኝ ኃይሎች ዉጊያ መሆኑ ግልፅ ነዉ።
|
በእነዚህ ወገኖች መካከልም የተጀመረዉ የሰላምድ ድርድር በያዝነዉ ሳምንት ዳግም ተጀምሯል።
|
እስካሁን በተካሄደዉ ድርድር የምስራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ መንግስታት ማለትም ሰላም ለማዉረድም ሆነ አዲሲቱን ሀገር ለማረጋጋት ያከናወነዉ እንዴት ይገመገማል
|
አንድሪዉ አታ አሳሞሃ ሂደቱን በሁለት ደረጃ ከፍለዉ ይመለከቱታል እስካሁን ያለዉን በሁለት ደረጃ ከፍሎ መመልከት ይቻላል።
|
የመጀመሪያዉ አካሄዱን ይመለከታል ተገቢዉን ሰዎች ይዘዋል ወይ የሚለዉ ነዉ።
|
በሁለተኛዉ የማየዉ ጥቅል መፍትሄዉን ነዉም ምክንያቱም በአሁኑ ወቅት የሆነ ማዕቀፍ ማየት ነበረብን።
|
በአንድ ወገን ለዉጤት የሚጠቅሙ ሰዎች ይዟል በሌላ ወገን ደግሞ ዉሳኔዉን የማስፈፀም አቅም አይታይም።
|
እናም እንደጠንካራ የአካባቢዉ ቡድን ተዋናዮቹ የተስማሙበትን እንዲያከብሩ የመግፋት አቅሙን አልተጠቀመም።
|
ሆኖም ካምፓላ የፕሬዝደንት ሳልቫ ኪርን ለመደገፍ ጦሯን እዚያ ካሰማራች ሰንብታለች።
|
የካምፓላ ወታደራዊ ኃይል እዚያ መገኘት ድርጅቱ ሰላም ለማዉረድ የሚያካሂደዉን ጥረት የማደናቀፉ ሁኔታ እንዴት ይታያል
|
እዉነታዉ ዩጋንዳ ዉስጥ ቁልፍ ሚና አላት በዚያዉ መጠን ደግሞ በግልፅ በማጥቃት በኩል ወገን ይዛ የሳልቫኪርን አስተዳደር ለመታደግ ድጋፍ እየሰጠች ነዉ።
|
እናም እንደሚመስለኝ ይህ የ ን ሕጋዊነት ዝቅ የሚያደርግ ነዉ።
|
ምክንያቱም ከማን ወገን ነዉ በሚል ከ በኩል ጥያቄዎችን ያስነሳል።
|
የረጲ ኃይል ማመንጫ ግንባታ እየተጠናቀቀ ነው ስዊዲን ቆሻሻ ከሌሎች ሀገሮች ማስገባት ሁሉ ጀምራለች፡፡
|
ስዊዲን ሚሊዮን ከሚጠጋው ህዝቧ የሚሰበሰበውን በመቶ ቆሻሻ በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ መልሳ ጥቅም ላይ ማዋሏ ነው የቆሻሻ ያለህ
|
የሀገሪቱ ይፋዊ ድረ ገጽ እንደሚጠቁመው ከየቤቱ ከሚሰበሰበው ቆሻሻ ውስጥ በመቶው ለኃይል ማመንጫነት ይውላል፡፡
|
በስዊዲን ቆሻሻን በማንደድ ሙቀት እና የኤሌክትሪክ ኃይልን የሚያመነጩ ተቋማት አሉ፡፡
|
አውሮፓዊቷ ሀገር የመጀመሪያውን እንዲህ አይነት ተቋም በዋና ከተማይቱ ስቶኮሆልም ያቋቋመችው እንደጎርጎሮሳዊው በ ነው፡፡
|
ኢትዮጵያ ከስዊዲን አንድ ምዕት አመት ዘግይታም ቢሆን መንገዱን ተያይዛዋለች፡፡
|
ከቆሻሻ ኃይል የሚያመነጭ ተቋም ለመገንባት ግንባታ ከጀመረች ሶስት ዓመት አለፋት፡፡
|
ቦታው ደግሞ የመጋቢት ሁለቱ አስደንጋጩ አደጋ ከደረሰበት አቅራቢያ ነው፡፡
|
በዚያ አዲስ አበባ በ ዓ ም ለደረቅ ቆሻሻ መጣያነት ስራ ያስጀመረችው የቆሻሻ መድፊያ ከእነ ክምር ቆሻሻው አለ፡፡
|
ረጲ የደረቅ ቆሻሻ ማመንጫ የተሰኘው አዲሱ ፕሮጀክት ግንባታው ወደ መገባደዱ ቢቃረብም ይህን ለዓመታት የተከማቸ ቆሻሻ ወደ ኃይል የሚለወጥ አይደለም፡፡
|
ይልቅስ ከአዲስ አበባ በየቀኑ ከሚሰበሰበው ወደ ሁለት ሚሊዮን ኪሎግራም ቆሻሻ ውስጥ በመቶውን ወደ ኤሌክትሪክ ኃይል የመቀየር እቅድ ያለው ነው፡፡
|
አቶ ሳሙኤል አለማየሁ የኃይል ማመንጫውን በመገንባት ላይ ያለው የካምብሪጅ ኢንዱስትሪስ የአፍሪካ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ናቸው፡፡
|
ቆሻሻዎቹን በደንብ አድርገን ውሃቸው ጠልሎ እንዲወጣ ካደረግን በኋላ ወደ ማንደጃ ውስጥ እንከታቸዋለን፡፡
|
ቆሻሻው እነዚህ ማንደጃዎች ውስጥ በ ዲግሪ ሴንትግሬድ ላይ ነው የሚነደው፡፡
|
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.